
-
Noble Amhara
- Senior Member
- Posts: 13724
- Joined: 02 Feb 2020, 13:00
- Location: Abysinnia
-
Noble Amhara
- Senior Member
- Posts: 13724
- Joined: 02 Feb 2020, 13:00
- Location: Abysinnia
Re: Lasta Wollo Fano Leader Fikru Muluye Surrenders to Baedan
Mesay Mekonnen
የብልጽግና ተዝካር በቁሙ ሲወጣ እንደማየት የሚያስደንቀኝ ነገር የለም። የጦር ካርታ በመዳፉ በሚል የተወደሰው፥ የአብይ አህመድ የጦር መሀንዲስ በሚል የሚሞካሸው ጄነራል ተስፋዬ አያሌው፥ እናትና ልጅን በአንድ ጊዜ ደፍሮ በፋኖ ሲፈለግ ጠፍቶ እጅ የሰጠን ግለሰብ ለመቀበል በዚህ ደረጃ ሽር ጉድ ማለታቸው በቁም ተዝካርን ከመብላት ተለይቶ የሚታይ አይደለም። ኮማንዶ ፍቅሩን በቅርበት አውቀዋለሁ። አሁን ይህን ጉድፉን የማነሳው ከድቶ ለብልጽግና እጅ ስለሰጠ አይደለም። ፋኖዎች አሁንም በወንጀል የተጨማለቁ መሪዎች ካሉ በቶሎ ቆርጠው ከድርጅቱ ማባረርና በህግ ተጠያቂ እንዲሆን ማድረግ እንዳለባቸው አጥብቄ ለማስገንዘብ በሚል ነው።
ኮማንዶ ፍቅሩ ከዚህ በፊት አራት ሴቶችን በመድፈር ወንጀል በፋኖ መንደር ከፍተኛ ውዝግብ የፈጠረ ጉዳይ እንደነበረና ለጊዜው ተድበስብሶ ያለፈበትን ክስተት አስታውሰዋለሁ። ፋኖ በዚህ ሰው የሚኮራ ሳይሆን አንገቱን የሚደፋበት ነው። በመጨረሻም እናትንና ልጃቸውን በአንድ ላይ ደፍሮ ሲፈለግ አምልጦ ላሊበላ በመግባት እጁን ሰጥቷል። ብልጽግና የእንደዚህ ዓይነት ወንጀለኛ መደበቂያ መሆኑን አስመስክሯል። ይህ ሰው የከሸፈ ጥይት ነው። ነገ ፍትህ ሲረጋገጥ በደፈራቸው ሴቶች ልክ የሚጠየቅ ይሆናል። ለጊዜው ድል የነጠፈበት ብልጽግና በዚህ ሰው እጅ መስጠት ጮቤ እየረገጠ ነው።
እዚህ ላይ አጥብቄ ማስታወስ የምፈልገው የኮማንዶ ፍቅሩን ግዙፍ ወንጀሎች ያነሳሁት ዛሬ እጅ በመስጠቱ አይደለም። አንድ ቀን ላፋጥጠው እንደምችል በግል ስልኩ ጽፌለት አስረግጬ ነግሬዋለሁ። እጅ ሰጥቶ ቀደመኝ እንጂ! የጄነራል ተስፋዬ አያሌው ነገር ግን አስገራሚ ነው። ስትራቴጂክ ድል ትቶ ችርቻሮ ውስጥ ገብቷል። እኔም ዘንድ ደውሎ ያደረገው ይሄንኑ ነበር። የከሰረ ነጋዴ የዱቤ ደብተሩን ያገላብጣል አሉ?! ውሃው ይሄዳል፥ አለቱ ይቀራል።
የብልጽግና ተዝካር በቁሙ ሲወጣ እንደማየት የሚያስደንቀኝ ነገር የለም። የጦር ካርታ በመዳፉ በሚል የተወደሰው፥ የአብይ አህመድ የጦር መሀንዲስ በሚል የሚሞካሸው ጄነራል ተስፋዬ አያሌው፥ እናትና ልጅን በአንድ ጊዜ ደፍሮ በፋኖ ሲፈለግ ጠፍቶ እጅ የሰጠን ግለሰብ ለመቀበል በዚህ ደረጃ ሽር ጉድ ማለታቸው በቁም ተዝካርን ከመብላት ተለይቶ የሚታይ አይደለም። ኮማንዶ ፍቅሩን በቅርበት አውቀዋለሁ። አሁን ይህን ጉድፉን የማነሳው ከድቶ ለብልጽግና እጅ ስለሰጠ አይደለም። ፋኖዎች አሁንም በወንጀል የተጨማለቁ መሪዎች ካሉ በቶሎ ቆርጠው ከድርጅቱ ማባረርና በህግ ተጠያቂ እንዲሆን ማድረግ እንዳለባቸው አጥብቄ ለማስገንዘብ በሚል ነው።
ኮማንዶ ፍቅሩ ከዚህ በፊት አራት ሴቶችን በመድፈር ወንጀል በፋኖ መንደር ከፍተኛ ውዝግብ የፈጠረ ጉዳይ እንደነበረና ለጊዜው ተድበስብሶ ያለፈበትን ክስተት አስታውሰዋለሁ። ፋኖ በዚህ ሰው የሚኮራ ሳይሆን አንገቱን የሚደፋበት ነው። በመጨረሻም እናትንና ልጃቸውን በአንድ ላይ ደፍሮ ሲፈለግ አምልጦ ላሊበላ በመግባት እጁን ሰጥቷል። ብልጽግና የእንደዚህ ዓይነት ወንጀለኛ መደበቂያ መሆኑን አስመስክሯል። ይህ ሰው የከሸፈ ጥይት ነው። ነገ ፍትህ ሲረጋገጥ በደፈራቸው ሴቶች ልክ የሚጠየቅ ይሆናል። ለጊዜው ድል የነጠፈበት ብልጽግና በዚህ ሰው እጅ መስጠት ጮቤ እየረገጠ ነው።
እዚህ ላይ አጥብቄ ማስታወስ የምፈልገው የኮማንዶ ፍቅሩን ግዙፍ ወንጀሎች ያነሳሁት ዛሬ እጅ በመስጠቱ አይደለም። አንድ ቀን ላፋጥጠው እንደምችል በግል ስልኩ ጽፌለት አስረግጬ ነግሬዋለሁ። እጅ ሰጥቶ ቀደመኝ እንጂ! የጄነራል ተስፋዬ አያሌው ነገር ግን አስገራሚ ነው። ስትራቴጂክ ድል ትቶ ችርቻሮ ውስጥ ገብቷል። እኔም ዘንድ ደውሎ ያደረገው ይሄንኑ ነበር። የከሰረ ነጋዴ የዱቤ ደብተሩን ያገላብጣል አሉ?! ውሃው ይሄዳል፥ አለቱ ይቀራል።
