Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
eden
Member+
Posts: 9997
Joined: 15 Jan 2009, 14:09

‘ጃዊሳ’ በሚል ፋኖ ላይ የተጀመረው የአራት ኪሎ ፕሮፓጋንዳ፣ ‘ፋኖ’ በሚለው ተቀይሮ የቀጠለውና የተፋፋመው ለምንድን ነው? | language is everything: Jawisa to FANO

Post by eden » 30 Mar 2024, 14:40

ያኔ የኦህዴድ-ብልፅግና አካሄድ ለዘብ ያለና ፋኖን ፊት ለፊት ከመቀጥቀጥ፣ ጃዊሳ በሚል የጥቂቶች የሽፍትነት አካሄድ አድርጎ የማሳየት ነበር. የአገዛዙ ቀመር ወዲህ ነው. ፋኖ ካልን ከህዝብ ያጣላናል ነው.

አሁን ግን፣ ጃዊሳ ማለቱን ትቶ፣ ፋኖ እያለ በቀንደኛ ካድሬዎቹ፣ ፕሮፓጋንዳውን እየሰራበት ነው

ብዙ ሰው ይህን የፕሮፓጋንዳ ሽፍት ያስተዋለ አልመሰለኝም? ለነገሩ ብዙ ግዜ ብዙ ሰው አያስተውልም. አገዛዙም የቆየው ለዚህ ነው.

እኔ ግን ይህ የፕሮፓጋንዳ ሽፍት ትልቅ እንደምታ አለው ባይ ነኝ.

አሁን ፋኖን ፋኖ ብሎ ፕሮፓጋንዳ፣ በስትራቴጂ ደረጃ እየሰራበት ይገኛል. ግን ፋኖ ደግሞ፣ በድፍን አማራ፣ ከዛም ባሻገር፣ የሚደገፍ የህዝብ አካል ነው.

ምን ይታይሃል/ሻል?



p.s. ቀንደኛ ካድሬዎቹ: ሲሳይ አጌና፣ ስዩም ተሾመ እንዲሁም ዘሃበሻ፣ ፈታ፣ ሃቅና ሳቅ እና መሃል ሜዳ.