DefendTheTruth wrote: ↑29 Jan 2024, 17:58
እንደ ስዩም ተሾመ አገላለፅ ከሆነ፣ ራስ ጎበና ዳጬ ለ አፄ ምንሊክ የወሉትን ዉለታ፣ የተከበሩ አቶ ደመቀ መኮንን መልሶታል ይለናል።
አፄ ምንሊክን የአማራ ጎጠኞች ና የተቀሩት የጊዜዉ መሳፍንቶች ኣናሰራም ብሎ ቸክሎ ስያስቸግሩዋቸዉ የቀርብ አጋዥ ራስ ጎበና ዳጬ ሆኖ ተገኙ፣ ሁለቱም ለዛሬይቷ ኢትዮጵያ ና ዝናዋ መሰረት ጥለዉ አለፉ።
በአቶ ደመቀ መኮንንም ላይ የዛሬዉ የአገሪቷ መሪ የሆኑት ዶር አቢዪ አህመድም ተመሳሳይ እገዛ በማግኝታቸዉ፣ የዛሬዉን ለዉጥ ማሳካት ችሎዋል። ደመቀም የተከበሩ አንጋሽ በመሆን ታሪካዊዉን ብድር መመለስ ችሎዋል፣ የአማራን ና የኦሮሞን ዘመን ተሻጋሪ አጋርነትንም ለዝንተአለማዊነቱ አፅድቆታል።
ታሪክ ራሷን ደግማለች። ጣላቶቿ አሁንም ከዉስጥም ከዉጪም እፍረት ተከናንቦ ወደ መጡበት ተመልሶዋል።
የሞት እንጋሾሽ፣ የሞት ወቃሾች ና እንዲሁም የሞት አርካሾች በምገባቸዉ ደረጀ ወርደዉ ወደ መጡበት ተመልሶዋል። አሜን!
ኣጼ ምኒልክ እና ራስ ጎበና ለዛሬይቱ ኢትዮጵያ መሠረት ጥለዋል ለማለትም በቃን። አሜን። አመን። አሙን። እንኳን ሃገር ጎጆ ማቆም ያለፋል።
ኣንድ የማልረሳዉ ክርክር ኣንዱ ራስ ጎበናን ሲወቅስ ኣንድ የአርሲ ሰዉ ራስ ጎበና ከእኛ ማዶ ቆሞ የነበረ ቢሆንም ጀግና ሰዉ ነበር ማለቱን ነዉ።
በዚህ ፍጥነት ኣዳኙን እና ነብዩንም ወደመጣችሁበት ተመለሱ። እኛ የሰለጠን ሕዝብ መሆናችንን እራሳችሁ መስክራችኋል እኮ የምትል ይመስላል።
ኢትዮጵያ፣ አማራ፣ እና ኦሮሞ ዉስጥ የትኛዉ ቃል ነዉ በታሪክ ዉስጥ ቀዳሚዉ?
ዳግማዊ ምኒልክ፣ ራስ ጎበና፣ እና ሌሎችም በታሪክ ኢትዮጵያን ያስቀደሙበት ተፈጥሮኣዊ ምክንያት ይኖር ይሆን?
ኣንድ ግዜ ያነበብኩኝ ታሪክ ደጃዝማች ኩምሳ ሞሮዳ ለዳግማዊ ምኒልክ በመቅረብ ራስ ጎበናን ከኣጼዉ ማራቅ ሞክረዉ ነበር ይላል። ይህ ኣሉባልታ ወይስ እዉነት ነዉ? እዉነት ከሆነ የደጃዝማቹንም ዉለታ ኣታሳንስባቸዉ እንጂ።
የአርሲዉ ነዺ ገመዳ በህይወቱ ዉስጥ ኣይሮፕላንም ይሁን ሄሊኮፕተር ኣንድም ቀን ቢሆን ተሳፍሮ ከመሬት መነሳቱ ይታወቃል? የሚታወቅ ከሆነ ያም ሌላ ታሪክ ይሆናል።