Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
TGAA
Member+
Posts: 5747
Joined: 07 Apr 2019, 20:34

የብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ጽ/ቤት ኃላፊ ኡመር ለማ መገደል እንደ ግርማ የሺ ጥላ የፖለቲካ ትርፍ ስሌለው ለዜና እንኳን አልበቃም ፤የብሄር ብሄረሰቦች የተበላ ቁማር

Post by TGAA » 10 May 2023, 02:20

በአፋር ክልል የብልፅግና ፓርቲ የወረዳ አመራር ተገደሉ

(አዲስ ማለዳ) ከአዳማ ወደ አዋሽ በሚወስደው መንገድ ላይ ከትላንት በስቲያ ቅዳሜ ሚያዚያ 28/2015 በተከፈተ ተኩስ በአፋር ክልል በገቢ ረሱ የሓንሩካ ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ጽ/ቤት ኃላፊ ኡመር ለማ መገደላቸውን የአፋር ክልል የብፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት አሳውቋል።

ኡመር “አሸባሪዎች በከፈቱት ተኩስ” ሕይወታቸውን ማጣታቸውን የገለጸው ጽሕፈት ቤቱ፤ በኃላፊው ድንገተኛ ሞት የተሰማውን ሀዘን ገልጿል።

ጽሕፈት ቤቱ ስለጥቃት አድራሾቹ ማንነት፣ ጥቃቱ በተፈጸመበት ወቅት በሌሎች ላይ ጉዳት ስለመድረሱና ስለተወሰደው እርምጃ በዝርዝር የገለጸው ነገር የለም።