የፋኖ ባለ 14 ነጥብ ምላሽ--- መታጠቅ መብታችን፤ በተለይ ደግሞ መንግሥት መር ጥፋት ባለበት ሁሉም እራሱን ለመጠብቅ መታጠቅ የገባዋል።
የፋኖ ባለ 14 ነጥብ ምላሽ--- መታጠቅ መብታችን፤ በተለይ ደግሞ መንግሥት መር ጥፋት ባለበት ሁሉም እራሱን ለመጠብቅ መታጠቅ የገባዋል። በመሰረቱ ማንም ዜጋ እራሱን ለመጠበቅ መሳርያ የመታጠቅ መብት አለው። ስለዚህ ፋኖን መሳርያህን ስጠን ማለት በእራሱ ህገ-ወጥ ነው። መሳርያ የሚጠይቀው ሃይል ወንጅል ለመፈጸም የተዘጋጀ መሆን አለበት። ሌላው ፋኖ መጠንቀቅ ያለበት ብልጽግና በሚጠራቸው ስብሰባዎች ላይ በቡድን ታዳሚ መሆን የለበትም። እየታደነ መሆኑን ማወቅ አለበት። ፋኖ እና ብልጽግና የሚወያዩባቸው መድረኮች የፋኖን አባላት ይሁን መሪዎች ደህንነት የጠበቀ መሆን አለበት።