Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Naga Tuma
Member+
Posts: 7429
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

ቅኔ ድሮ እና ዘንድሮ፤ ያለኳስ ጫወታ

Post by Naga Tuma » 07 Sep 2022, 17:18

የድሮ ሰዉ የሰዉ ቅኔ ይጠቅስልሃል።

ኣንዳንዱ የዘንድሮ ሰዉ ቅኔ ጥቀስ ሲባል እኔዉ እቀኝልሃለሁ ይላል። በጀ። ይለምልም። እንዴት ባህል እንደሆነ ኣላዉቅም። መክማክሳም ተመሳሳይ ይመስለኛል።

የድሮ ቅኔ መቼ እንደተቀኘ በሰፊዉ የተመዘገበ ኣይመስለኝም። አለቃ ገብረሃና ብሻን እንጠጣለን፣ ብሻን እንበላለን ብሎ ነበር ባይ እንጂ የቀጠነዉ ወጥ ማን ቤት እና መቼ እንደነበረ የተመዘገበ ኣይመስለኝም።

የዘንድሮ ቀኚዎች ቅኔዎቻችሁን ለመጪዉ ትዉልድ ብትመዘግቡ ምን ይመስላችሁዋል?

ከኣሁን በፊት ሰዉ በቁሙ ከመሞት ለምን ቆሞ ኣይሞትም ብዬ ኣልፌኣለሁ። ኣሁን ኣንድ ቅኔን ለኣንድ ባልደረባዬ ማስረዳት ኣስቸግሮኛል።

ኳስ ሳይይዝ ሜዳ ገብቶ ልጫወት ባይ ባልደረባዬን ቅኔ ማስተማር ኣስቸገረኝ። እስከኣሁን ሰማንያ ስምንት ጊዜ ያህል ያለኳስ ሜዳ ገብቶ ጫወታ የለም እና እንካ ኳስ ብዬዋለሁ። ያጋኛትን ኳስ ወድያዉ ይጦልዛል። በእግሩ ሳይሆን በኣፉ። ከዛ ኣሁንም መጥቶ ተጦለዝኩ ይለኛል። በዚህ ያሳዝናኛል። እንካ ያልኩህ ኳስ እንዴት ሽዉ ይላል ብዬ ኣፍእላፊ እንዳልናገረዉ ሰጋሁ። ጋጠወጥ ብሎ ይሸሸል ብዬ። ምን ይሻላል እያልኩ ኣየዋለሁ። ኳስ ፈልገህ ያዝ፣ እንደኳስ ኣትጦለዝ ብሎት የሚሰማዉ በተገኘ።