3h ·
እስከ መቼ????
============
በተደጋጋሚ ተናግርያልሁ:: አሁንም እደግመዋለሁ:: ኦሮሞ በስሜን ኢትዮጵያ በሚደረጉ ጦርነቶች ከአሁን በኅላ በፍፁም መሳተፍ እና ልጆቹን መገበር እና ማዋረድ የለበትም:: በህይወት ዘመነ ሶስት ዘግናኝ እና ኢፍትሀዊ የሆኑ ጦርነቶች በሴሜን የሀገሪቱ ክፍል ሲካሄድ አይቻለሁ:: 17 አመት በደርግ ዘመን በትግራይ እና ኤርትራ, በኢህአዴግ በኢትዮ-ኤርትርያ ጦርነት ወቅትና ድጋሚ አሁን በትግራይ በተደረገው አላስፈላጊ ጦርነት::በእነዚህ ጦርነቶች በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ጉዱት ደርሶባቸዋል; በመቶ ሺዎች ህይወታቸው አጥቶአል:: ስለዚህ የኦሮሞ ደሃ ልጆች የአምባገነኖችን ስልጣን ለማስጠበቅ መሞት እና መዋረድ የለባቸውም:: ሌሎችም የኢትዮጵይ ብሔር ብሔረሰቦች ልጆቻቸውን ወደዚህ አይነት ጦርነቶች መላክ የለባቸውም:: ይህ የአደባባይ ውርደት public humiliation መቀጣጫ ሊሆናቸው ይገባል::
እነዚህ በፎቶግራፍ የሚትመለከቱት ዛሬ መቀሌ ላይ አንገት ድፍተው እና ተዋርደው ሲነዱ የነበሩ; አብይ ,ኢሳያስ እና ሊህቃን elites ( የአማራ, ለሆድ አደር ኦሮሞ እና የሀይማኖት ሊህቃን) ወደ ሞት የላኳቸው ናቸው:: ከመጀመሪያው እምብ ለጦርነት ብለን ነበር:: ስሞኑን ደስ ያለኝ ነገር "ባለፉት ወራት ወጣቱ መከላከያን እንዲቀላቀል ጥሪ አቅርበን ያገኘነው ሰው ብዛት ግን 5 ሺ ብቻ ነው!" የሚል ዘና ስስማ ነው:: ወጣቱ ድምፅችንን እየስማ ነው:: አምስት ሺ እንድያውም ብዙ ነው:: ከአሁን በኃላ 0 ነው መሆን ያለበት:: አብይ ከፍለገ ከቤቱ ይጀምር::: ልጁን ይላክ:: እነርሱ ልጆቻቸውን በአሜሪካ እና አውሮፖ ያስተምራሉ:: የድሃው ልጅ ግን ሄዶ ለእነርሱ ይሞታል ይዋረዳል:: እስከ መቼ?? ይህ በእኛ ትውልድ መቆም አለበት::
እግዚአብሔር ህዝብን ይጠብቅ::
ቄስ ተመስገን





