Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
sarcasm
Senior Member
Posts: 11594
Joined: 23 Feb 2013, 20:08

እነዚህ ለእልቂት እየተማገዱ ያሉትን ወጣቶች እንታደግ

Post by sarcasm » 29 Jun 2021, 19:34

እነዚህ ለእልቂት እየተማገዱ ያሉትን ወጣቶች እንታደግ
==================================
በስሜን ኢትዮጵያ የሚደረገውን ጦርነት መቃወም የህይወተ ዘመነ Mission አድርግያለሁ:: ምክንያቱም በተደጋጋሚ እንደተናገርኩኝ በህይወት ዘመነ እነሆ ሶስት ዘግናኝ, አላስፈላጊ እና ኢፍትሀዊ ጦርነቶችን አይቻለሁ:: በእነዚህ ጦርነቶች በርካታ የክፍል ጎደኞቼን, ጉሮበቶቼን እና የእድሜ እኩዮች የሚሆኑኝን ወጣቶችን አጥቻለሁ::

ታዳያ ዛሬም አብይ አህመድ ከብር ሸለቆ ማስልጠኛ በአግባብ ስልጠና እንኳን ወስደው ያልጨረሱትን ወጣች "አስመርቅያለሁ" በማለት ለጦርነት ሊማግዳቸው ተነስቶአል:: ባለፉት ሳምንታት በትግራይ የነበረው ኃይል ሙሉ በሙሉ ሲመታ ዛሬ ሌሎችን ለማገዶ እያቀረበ ነው::በዚህ ማስልጠኛ ውስጥ ልጆች ያላችሁ, ዘመዶች የሆናችሁ, ጎሮበቶች የሆናችሁ, እነዚህን ልጆች ከሞት ተደጉ:: በተለይ ደግሞ የኦሮሞ ልጆች; ለሃምሳ አመት ልጆቻችንን ገብረናል; በማይመለከተን ጦርነት; አሁን በቃ:: ይህ አዙሪት ማቆም አለበት:: ለኦሮሚያ ልዩ ኃይል, ለኦሮሚያ ፖሊስ አባላት, በመከላከያ ስራዊት ውስጥ ላላቹ የኦሮሞ ተወላጆች በሙሉ; ከህዝባቹ ከኦሮሞ ህዝብ ጎን የምትቆሙበት ጊዜ አሁን ነው:: የትግራይ ጦርነት ሲጀመር ይህ ጦርነት አይመለከታችሁን ስል ነበር::ራሳችሁን የምታድኑበት የመጨረሻው እድል አሁን ነው::

ቄስ ተመስገን


Please wait, video is loading...