Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Ejersa
Member
Posts: 3978
Joined: 05 Nov 2019, 10:39

‹‹መሬቱን እንጅ እናንተን አንፈልጋችሁም ተብለናል›› እስረኞች!

Post by Ejersa » 11 Dec 2020, 18:18

ባሕር ዳር፡ ታኅሣሥ 02/2013 ዓ.ም (አብመድ) በማንነታቸው እና በፖለቲካ ልዩነታቸው የታሰሩ እና ሊረሸኑ የነበሩ 64 እስረኞች በመከላከያ ሰራዊት ነፃ ወጥተዋል፡፡
በሕጋዊ መንገድ የማንነት ጥያቄ ያነሱ አማራዎች በትግራይ ክልል የተለያዩ ማጎሪያ ቦታዎች ታስረው እንደነበር በተደጋጋሚ ሲነሳ ቆይቷል፡፡ መንግስት በትግራይ ክልል የወሰደውን ሕግ የማስከበር ርምጃ ተከትሎም ወራሪው፣ ተስፋፊውና አሸባሪው ትህነግ 15 ሺህ 800 እስረኞችን ወደተንቤን ዓቢ ዐዲ የምድር ውስጥ ማጎሪያ ቤቶች አሽሽቷቸውም ነበር፡፡

ከጊዜ ወደ ጊዜ ሕግ የማስከበሩ ርምጃ እየጠነከረ መምጣቱን ተከትሎ ሕገ ወጡ ቡድን መውጫ መግቢያ ሲያጣ በማንነታቸው እና በፖለቲካ ልዩነታቸው ለእስር የተዳረጉ 64 ሰዎች ለግድያ ተለይተው ሌሎቹ ከእስር ተለቀቁ፡፡

ለግድያ የተዘጋጁት 64 የማንነት እና የፖለቲካ እስረኞችም ወራሪው፣ ተስፋፊውና አሸባሪው ትህነግ በመከላከያ ሰራዊት በደረሰበት ጥቃት ከለቀቃቸው በኋላ በሰራዊቱ ታጅበው መቀሌ ሲገቡ አነጋግረናቸዋል፡፡

የወልቃይት ነዋሪ የሆነው እና የማንነት ጥያቄ በማንሳቱ ብቻ ለ14 ዓመታት በእስር የተሰቃየው ስማቸው ተካልኝ የሞት ፍርድ ተበይኖበት እንደነበር ነግሮናል፡፡ ጥፋቴ ያለውን ሲነግረንም የወልቃይት አማራዎች እየተፈናቀሉ በሰፈራ ስም ከሌሎች አካባቢዎች ለመጡ ሰፋሪዎች ሰፋፊ መሬት መሰጠቱን መቃዎሙ ነበር፡፡ በእስር ቤት ውስጥ በእርሱ እና መሰል ጓደኞቹ በርካታ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ይፈፀም ነበር ያለው ስማቸው ከምንም በላይ የሚያመው ግን ሊያስወግዱት የፈለጉትን ሰው ሰበብ ፈጥረው ለብቻው ካሰሩ በኋላ ገድለው ራሱን አጠፋ ብለው የሚያስወሩት ነገር ነበር ይላል፡፡

ከሁለት ዓመታት ከስድስት ወራት በፊት ሃገራዊ ለውጡን ተከትሎ የራያ ጥሙጋ አካባቢ ተወላጆች የማንነት ጥያቄያችን ይከበር በሚል በግልፅ አደባባይ ወጥተው ነበር፡፡ በወቅቱ ከ54 በላይ ተወላጆች በህገ ወጡ ቡድን በተተኮሰ ጥይት ሲጎዶ በርካቶች ደግሞ ወደቆቦ ሸሽተው ጊዜ አሳልፈዋል፡፡ ‹‹መሬቱን እንጅ እናንተን አንፈልጋችሁም ተብለናል›› የሚለው ብርሃኑ በላይ ተፈራ በወቅቱ በትህነግ ከሚፈለጉ የመብት ጠያቂዎች እና የትውልድ ቀየውን ለቀው ከሸሹት መካከል አንዱ ነበር፡፡ ከሦስት ወራት በኋላ አገር አማን ሆኗል ብሎ ወደቀየው መመለሱን ተከትሎ በምሽት ከቤቱ ታፍኖ ተወሰደ፡፡

ብርሃኑ በህገ ወጡ የትህነግ ቡድን ከታፈነ በኋላ በቀድሞው የጣሊያን ምሽግ አምባላጌ የጀመረው እስር ከአምባለጌ እስከ መሆኒ፤ ከማይጨው እስከ ባዶ ስድስት፤ ከመቀሌ እስከ ዓቢ አዲ ያላንከራተቱበት ማረሚያ ቤት ያላስተናገደው ግፍና መከራ የለም፡፡ እነብርሃኑ የመጨረሻ የሞት ቀነ ቀጠሮ ተቆርጦላቸው ሕዳር 23/2013 ዓ.ም ለግድያ ወደ ተንቤን ገዛ ተጋሩ እንደወሰዷቸውም ይናገራል፡፡ ነገር ግን የተንቤን ማረሚያ ቤት ኃላፊ ባለቀ ስዓት በእነዚህ ሰዎች ደም እጃችን አናጨቀይም ማለቱን ተከትሎ በገዳዮች መካከል ልዩነት ተፈጠረ፡፡ በዚህ ውዝግብ መካከል ነበር የሰማይ ጀቶች የምድር ኮማንዶዎች ወደ አካባቢው መቃረባቸው የተሰማው፡፡

የመንግስት ህግ አስከባሪዎች ወደቦታው መቃረባቸውን ተከትሎም የሕገ ወጡ ቡድን አባላት እግሬ አውጭኝ ብለው አካባቢውን ሲለቁም ለሞት የተዘጋጁት ንጹሃን የነጻነት ብርሃን ወጣላቸው፡፡ የሃገር መከላከያ ሰራዊትም አስፈላጊውን እንክብካቤ በማድረግ መቀሌ እንዳደረሳቸው ነግረውናል፡፡

እስረኞቹ ህይዎታቸውን ለታደጋቸው እና አስፈላጊውን እንክብካቤ ላደረገላቸው የመከላከያ ሃይል ምስጋና አቅርበው ለዘመናት የታገሉለት ዓላማ ዳር እንዲደርስ አሁንም ከመንግስት ጎን በመሆን እንደሚታገሉ ተናግረዋል፡፡

ዘጋቢ፡- ታዘብ አራጋው - መቀሌ
Please wait, video is loading...

Za-Ilmaknun
Member
Posts: 4487
Joined: 15 Jun 2018, 17:40

Re: ‹‹መሬቱን እንጅ እናንተን አንፈልጋችሁም ተብለናል›› እስረኞች!

Post by Za-Ilmaknun » 11 Dec 2020, 19:16

It is unsurprising that TPLF has only been interested in the lands of wolQait and Raya. It has done everything unimaginable to humanity to realize that objective. The mass graves are testament to the naked barbarism of TPLF and its cadres. Time will tell if these people are going to have peace of mind in their entire existence.

What is more disturbing is those who are still sympathetic for such evil groups. We can only give meaning to such solidarity when we see it from the point of view of what both groups are after. The preach about fake federalism all along vying to swallow everything and anything that doesn't look like them or that doesn't belong to them. They both value human lives as nothing but a means to expend to achieve their evil agenda. They preach diversity while all along they are more interested in imposing their identity and values on to others. They blame the none existing past to justify their present-day barbarism and cannibalism. They talk about constitution at the same time the do things obviously are against what is in the text of their constitution. They talk about Ethiopian flag when in fact they never are willing to carry it...unless of-course when it suits the pretentions.

They are now being exposed naked and gasping their last breath. Please know that TPLF shall never come back to life!!!

Hameddibewoyane
Member
Posts: 3890
Joined: 25 Sep 2019, 02:42

Re: ‹‹መሬቱን እንጅ እናንተን አንፈልጋችሁም ተብለናል›› እስረኞች!

Post by Hameddibewoyane » 11 Dec 2020, 20:24

:shock: :shock: :shock: :shock:
Ejersa wrote:
11 Dec 2020, 18:18
ባሕር ዳር፡ ታኅሣሥ 02/2013 ዓ.ም (አብመድ) በማንነታቸው እና በፖለቲካ ልዩነታቸው የታሰሩ እና ሊረሸኑ የነበሩ 64 እስረኞች በመከላከያ ሰራዊት ነፃ ወጥተዋል፡፡
በሕጋዊ መንገድ የማንነት ጥያቄ ያነሱ አማራዎች በትግራይ ክልል የተለያዩ ማጎሪያ ቦታዎች ታስረው እንደነበር በተደጋጋሚ ሲነሳ ቆይቷል፡፡ መንግስት በትግራይ ክልል የወሰደውን ሕግ የማስከበር ርምጃ ተከትሎም ወራሪው፣ ተስፋፊውና አሸባሪው ትህነግ 15 ሺህ 800 እስረኞችን ወደተንቤን ዓቢ ዐዲ የምድር ውስጥ ማጎሪያ ቤቶች አሽሽቷቸውም ነበር፡፡

ከጊዜ ወደ ጊዜ ሕግ የማስከበሩ ርምጃ እየጠነከረ መምጣቱን ተከትሎ ሕገ ወጡ ቡድን መውጫ መግቢያ ሲያጣ በማንነታቸው እና በፖለቲካ ልዩነታቸው ለእስር የተዳረጉ 64 ሰዎች ለግድያ ተለይተው ሌሎቹ ከእስር ተለቀቁ፡፡

ለግድያ የተዘጋጁት 64 የማንነት እና የፖለቲካ እስረኞችም ወራሪው፣ ተስፋፊውና አሸባሪው ትህነግ በመከላከያ ሰራዊት በደረሰበት ጥቃት ከለቀቃቸው በኋላ በሰራዊቱ ታጅበው መቀሌ ሲገቡ አነጋግረናቸዋል፡፡

የወልቃይት ነዋሪ የሆነው እና የማንነት ጥያቄ በማንሳቱ ብቻ ለ14 ዓመታት በእስር የተሰቃየው ስማቸው ተካልኝ የሞት ፍርድ ተበይኖበት እንደነበር ነግሮናል፡፡ ጥፋቴ ያለውን ሲነግረንም የወልቃይት አማራዎች እየተፈናቀሉ በሰፈራ ስም ከሌሎች አካባቢዎች ለመጡ ሰፋሪዎች ሰፋፊ መሬት መሰጠቱን መቃዎሙ ነበር፡፡ በእስር ቤት ውስጥ በእርሱ እና መሰል ጓደኞቹ በርካታ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ይፈፀም ነበር ያለው ስማቸው ከምንም በላይ የሚያመው ግን ሊያስወግዱት የፈለጉትን ሰው ሰበብ ፈጥረው ለብቻው ካሰሩ በኋላ ገድለው ራሱን አጠፋ ብለው የሚያስወሩት ነገር ነበር ይላል፡፡

ከሁለት ዓመታት ከስድስት ወራት በፊት ሃገራዊ ለውጡን ተከትሎ የራያ ጥሙጋ አካባቢ ተወላጆች የማንነት ጥያቄያችን ይከበር በሚል በግልፅ አደባባይ ወጥተው ነበር፡፡ በወቅቱ ከ54 በላይ ተወላጆች በህገ ወጡ ቡድን በተተኮሰ ጥይት ሲጎዶ በርካቶች ደግሞ ወደቆቦ ሸሽተው ጊዜ አሳልፈዋል፡፡ ‹‹መሬቱን እንጅ እናንተን አንፈልጋችሁም ተብለናል›› የሚለው ብርሃኑ በላይ ተፈራ በወቅቱ በትህነግ ከሚፈለጉ የመብት ጠያቂዎች እና የትውልድ ቀየውን ለቀው ከሸሹት መካከል አንዱ ነበር፡፡ ከሦስት ወራት በኋላ አገር አማን ሆኗል ብሎ ወደቀየው መመለሱን ተከትሎ በምሽት ከቤቱ ታፍኖ ተወሰደ፡፡

ብርሃኑ በህገ ወጡ የትህነግ ቡድን ከታፈነ በኋላ በቀድሞው የጣሊያን ምሽግ አምባላጌ የጀመረው እስር ከአምባለጌ እስከ መሆኒ፤ ከማይጨው እስከ ባዶ ስድስት፤ ከመቀሌ እስከ ዓቢ አዲ ያላንከራተቱበት ማረሚያ ቤት ያላስተናገደው ግፍና መከራ የለም፡፡ እነብርሃኑ የመጨረሻ የሞት ቀነ ቀጠሮ ተቆርጦላቸው ሕዳር 23/2013 ዓ.ም ለግድያ ወደ ተንቤን ገዛ ተጋሩ እንደወሰዷቸውም ይናገራል፡፡ ነገር ግን የተንቤን ማረሚያ ቤት ኃላፊ ባለቀ ስዓት በእነዚህ ሰዎች ደም እጃችን አናጨቀይም ማለቱን ተከትሎ በገዳዮች መካከል ልዩነት ተፈጠረ፡፡ በዚህ ውዝግብ መካከል ነበር የሰማይ ጀቶች የምድር ኮማንዶዎች ወደ አካባቢው መቃረባቸው የተሰማው፡፡

የመንግስት ህግ አስከባሪዎች ወደቦታው መቃረባቸውን ተከትሎም የሕገ ወጡ ቡድን አባላት እግሬ አውጭኝ ብለው አካባቢውን ሲለቁም ለሞት የተዘጋጁት ንጹሃን የነጻነት ብርሃን ወጣላቸው፡፡ የሃገር መከላከያ ሰራዊትም አስፈላጊውን እንክብካቤ በማድረግ መቀሌ እንዳደረሳቸው ነግረውናል፡፡

እስረኞቹ ህይዎታቸውን ለታደጋቸው እና አስፈላጊውን እንክብካቤ ላደረገላቸው የመከላከያ ሃይል ምስጋና አቅርበው ለዘመናት የታገሉለት ዓላማ ዳር እንዲደርስ አሁንም ከመንግስት ጎን በመሆን እንደሚታገሉ ተናግረዋል፡፡

ዘጋቢ፡- ታዘብ አራጋው - መቀሌ
Please wait, video is loading...

Post Reply