በጁላይ 1 አዲስ አበባ በቄሮ ከመቃጠል ያዳናት እስክንድር ነጋ ያደራጀው የሸገር ወጣት ነው ! አቢይ አህመድ ካዲስ አበቤ ጋር ችግር ውስጥ ነው !!
እኔ ባሁን ሰአት ስንት ሰው የኦሮሞ ፖሊሶችን አምኖ ይጠብቁኛል ብሎ ማታ እንደ ሚተኛ አላቅም ። ኢትዮጵያዊያን በኦሮም ፖሊሶች ላይ ምን ያህል እምነት እንዳጡ በጥናት መታየት አለበት ። ግ ን አንድ በሃቅ የተረጋገጠ ነገር አለ። ዝዋይ ፣አርሲ፣ ሻሸመንኔ፣ ጂማ በቄሮ የነደዱት እንደ አዲስ አበባ ተደራጅቶ ራሱን የሚጠብቅ ወጣትና ሕዝብ ስለሌላቸው ነው። ይህን ሃቅ በንጹ ልቦና ላስተዋለ አዲስ አበባን ከመንደድ ያዳናት እስክንደር ያደራጀው ወጣት ነው ። ሃቁ ይህ ሆኖ ሳለ እስክንደርን ከነፍሰ ገዳዩ ጃዋር ጋር አብሮ ማሰር አቢይ ካዲስ አበባ ጋር ያለውን ግዙፍ ችግር ፍንትው አድርጎ ያሳያል ።