Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum

Wedi
Member+
Posts: 8600
Joined: 29 Jan 2020, 21:44

Re: ዳውድ ኢብሳ ከስልጣን ወርደዋል ወይስ አልወረዱም? የኦነግ የአመራር ውዝግብ

Post by Wedi » 27 Jul 2020, 16:04

''የኦነግ ትግል ወራሽ ቲም ለማ እንጂ ዳውድ ኢብሳ አይደለም"
Please wait, video is loading...

Abere
Senior Member
Posts: 14876
Joined: 18 Jul 2019, 20:52

Re: ዳውድ ኢብሳ ከስልጣን ወርደዋል ወይስ አልወረዱም? የኦነግ የአመራር ውዝግብ

Post by Abere » 27 Jul 2020, 16:15

ለመሆኑ ኦነግ ሥልጣን አለው እንዴ?

Horus
Senior Member+
Posts: 40315
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ዳውድ ኢብሳ ከስልጣን ወርደዋል ወይስ አልወረዱም? የኦነግ የአመራር ውዝግብ

Post by Horus » 27 Jul 2020, 16:37

አበረ
ቁልፍ ጥያቄ ነው ያነሳሃው ! አዲስ ሃረግ በዚያ ጥያቄ ላይ ልከፍት ስል ቀድመህ ቁጭ አደረከው! በትክክል የስልጣን ትንተና የሌለው የፖለቲካ ትንተና ባዶ ነው። ማለትም ስለ ፖልቲካ ካወራን በቀጥታ ስለ ስልጣን ወይም የፖለቲካ ሃይል ማውራት አለብን። ያ ካልሆነ ግዜያችን ነው የምናባክን!

የፖለቲካ ስልጣን ወይም ሃይል ማለት መንግስት ነክ ነገሮችን የመወሰን ብሎም የመፈጸም ሃልይ ጉልበት ማለት ነው። ማ ምን ያገኛል? ማ ምን ማድረግ አለበት? ማ ምን ያደርጋል? ማድረግ አይችልም? ወዘተ የመወሰን ብሎም ያን ወሳኔ ተግባራዊ የማድረግ፣ የማስደረግ ሃይል ነው ስልጣን የምንለው ! ስለዚህ ልክ እንዳልከው ዳዉድ ኢብሳን በነዚህ መለከያዎች መፈተሽ አለብን ።

ኦነግ አንድ የመንግስትም ሆነ ሶሺያ፣ ክልላዊም ሆነ ቀበሌያዊ የፖለቲካ ስልጣን የሌለው አንድ ፓርቲ ወይም ድርጅት ወይም ማህበር ነው ። የኦነግ አባልት ያንድ ማህበር አባልት ናቸው፣ በቃ ! እነሱ አባልቾቻውን የሚያስተዳድር በአገሩ ሕግ መሰረት የተጻፈ ሕገ ማህበር ይኖራቸዋል ። ማነው ሊቀ መንበር፣ ገንዘብ ያዝ፣ ወዘተ ። ይህን ሕገ ማህበር በትክክል ስራ ላይ ማዋል ወይ መጣሱ የሚከታተለው የምርጫ ቦርድ ነው ። ከዚያ ባልፈ የመንግስት ስልጣን ያልያዘን የፖለቲካ ፓርቲም ሆነ የሲቪል ማህበር እንደ መንግስት ወስዶ ከስልጣን ወረደ፣ መፈንቅል ተካሄደበት ምናምን የሚሉት ልቅ አነጋገሮች የድንቁርና ማሳያዎች ናቸው።

ዳዉድ አብሳ በኢትዮጵያ መንግስት ወስጥ በምንም ደረጃ ምንም አይነት ስልጣን የለውም ። ይህ ሁሉ ድራማ በአንድ ድርጅት ወስጥ ባሉ አባላቱ መካከል ያለ ድራማ ነው !!!

ግሩም ጥያቄ !

Abere
Senior Member
Posts: 14876
Joined: 18 Jul 2019, 20:52

Re: ዳውድ ኢብሳ ከስልጣን ወርደዋል ወይስ አልወረዱም? የኦነግ የአመራር ውዝግብ

Post by Abere » 27 Jul 2020, 16:55

Horus,

የህዝባችን ችግር እኮ ማን እንኳን እንዴ ሚመራው ፈፅሞ አያውቅም። ዝም ብሎ ብቻ ይነዳል - ዝም ብሎ የሚሄድ ደግሞ እንዴ በግ ሌባ ተከትሎ ይሄዳል። ኦነግ ሥልጣን አለው ሲባል እኮ ይህን አሥርት ዓመታት የመግደል፣የማፈናቀል፣ የሽብር ወዘተ የማይከሰስ እና የማይገስስ መብት አለው ማለት ነው። ይህን ሥልጣን ማነው የሰጠው - ህዝብ አይደለም። ሥልጣን ካለ ደግሞ ተጠያቂነት አለ። ብቻ ገና ከጥንታዊው የጉልቤው አስተሳሰብ እና ልማድ አዲሱ ትውልድ እንኳን አልተመረም። ብጥንት ጊዜ እንኳን በህግ አምላክ ካለ ጉልቤው ወይም አጤ በጉልበቱ - ፈሪሃ እግዚአብሄር አለው - ያሁኑ እኮ አውሬ ነው።
አንድ የሰማሁት እውነት ላካፍልህ። አንድ መልቲ ማህተም አስቀርፆ የወረዳ አስተዳዳሪ በወቅቱ የሌለበት ቦታ ይሄድ እና ለወረዳው ህዝብ ከክፍለ ሀገር ተሹሜ መጥቻለሁ ይሄው ማህተሙ ማረጋገጫዬ ብሎ ዋሽቶ አንድ ሰሞን የወረዳ ገዥ ነበር ሲባል ሰምቻለሁ። ከዚህ ዓይነት ህዝብ የተገኜው ትውልድ አሁን እንደዛው ያስባል።

Post Reply