Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
AbebeB
Member+
Posts: 7694
Joined: 15 Oct 2016, 10:31

ያለምርጫ የተሰየመው የምርጫ ቦርድ መብትና ግዴታውን አላወቀም ነው ሲሉ ምሁራንና መኮንኖች በየዘርፋቸው ገለጹ፡፡

Post by AbebeB » 25 Jun 2020, 15:35

ያለምርጫ የተሰየመው የምርጫ ቦርድ መብትና ግዴታውን አላወቀም ነው ሲሉ ምሁራንና መኮንኖች በየዘርፋቸው ገለጹ፡፡



ግና መከላከያ ፊታቸው ላይ ቀርቦ በጊዜ ገለል በሉ እያላቸው ነው፡፡



የምሁራን አስተያዬት

1. የምርጫ ቦርድ፣ ምርጫ የማስፈጸም ግዴታ እንጂ ምርጫ የማገድ ሥልጣን አልተሰጠውም።

2. አንቀጽ 102፣ አገራዊው (“ብሔራዊ” ) ምርጫ ቦርድ ስለ መቋቋሙ፣ ስለ አባላቱ አሿሿም፣ እና ምርጫን በገለልተኝነት ለማስፈጸም ስላለበት ኃላፊነት ይደነግጋል እንጂ፣ ምርጫን ሁሉ የማስፈጸም ሥልጣን በብቸኝነት (exclusively) ለዚህ ተቋም ተሰጥቶታል አይልም።

3. “ብሔራዊ” ምርጫ ቦርድ በአንቀጽ 102 መሠረት ተቋቁሟል ብሎ ማለት፣ ምርጫን የማስፈጸም ሥራ በፌደራል መንግሥቱ የሥልጣን ወሰን ሥር ነው (በመሆኑም ክልሎች ምርጫን በማስፈጸም ጉዳይ ላይ ምንም ሥልጣን የላቸውም) ማለት አይደለም።

4. “ብሔራዊ” ምርጫ ቦርድ ይኖራል ማለት፣ በክልሎቹ ውስጥ፣ በክልሎቹ ሕገ-መንግሥታት ወይም አግባብነት ባላቸው ክልላዊ አዋጆች አማካኝነት፣ ክልላዊ የምርጫ አስፈጻሚ አካል ማቋቋም አይቻልም ማለት አይደለም።

5. ክልላዊ ምርጫን ለማካሄድ፣ “የብሔራዊ” ምርጫ ቦርድ ተጠይቆ፣ በፖለቲካ ወገንተኝነት ምክንያት አላስፈጽምም ካለ፣ ሕገ-መንግሥታዊ ግዴታውን አልተወጣም፣ ወይም ሊወጣ አልፈለገም ማለት ነው። ለዚህም፣ ተጠያቂ ሊደረግ ይገባዋል።

6. “ብሔራዊ” ምርጫ ቦርድ፣ በክልሎች ውስጥ ምርጫ የማስፈጸም ግዴታውን አልወጣም በማለቱ ምክንያት፣ ክልሎች በራሳቸው የምርጫ አስፈጻሚ አካል አማካኝነት ምርጫ ለማከናወን የሚያደርጉትን ጥረት፣ ማንኳሰስ፣ ለማገድ መሞከር፣ እና ሕጋዊ እውቅና እንደሌለው በማስመሰል መግለጫ መስጠት፣ ምርጫን ማወክ በመሆኑ፣ በወንጀል የሚያስጠይቅ ተግባር ነው።

7. የፌደራል “መንግሥቱ” ምርጫ የማድረግ ግዴታውን መወጣት ባለመፈለጉ ብቻ፣ የክልሎችን የምርጫ ሂደት ማስተጓጎል አይችልም። መሞከርም፣ ወንጀል ነው። በሕግ አግባብ ተከባብሮ የመኖር ግዴታውንም እየዘነጋ መሆኑም ሊነገረው ይገባል። በፌደራሉ ሕገ-መንግሥት፣ አንቀጽ 50(8) በተደነገገው መሠረት፣ የፌደራል መንግሥቱ የክልሎችን ሥልጣን፣ ክልሎችም የፌደራሉን መንግሥት ሥልጣን፣ ማክበር ይገባቸዋልና።

8. ሰሞኑን፣ አንዳንድ “የአዲስ አበባ ከተማ ጠበቆች” (ሕግ የማያውቁ የሕግ ባለሙያዎች) በ”አንዳንድ” የ FM ሬድዮ ስርጭቶች ላይ፣ “የፌደራል መንግሥቱ፣ ምርጫ በሚያደርጉ ክልሎች ላይ እርምጃ መወሰድ አለበት” ሲሉ የለገሱት ምክር፣ ምንም የሕግ መሠረት የሌለውና ኃላፊነት የጎደለው ንግግር ነው።

9. እነዚህ “በአንዳንድ” የFM ሬድዮ ስርጭቶች ላይ የቀረቡ “አንዳንድ የከተማው ጠበቆች፣” የትግራይ ክልል ምርጫ ካካሄደ፣ (ሕገ-ወጡ) “የፌደራል” መንግሥት”፣ ከፌደሬሽን ምክር ቤት የፌደራል ጣልቃ-ገብነት ትዕዛዝ አስወጥቶ፣ ትግራይን በፌደራል ኃይሎች ማጥቃት አለበት ሲሉ ተደምጠዋል። (ይህቺ እንኳን፣ የግጭትን ውጤት የማያውቁ የከተማ ነገረ-በሎች ከንቱ ትንኮሳ ነች ብለን ልንተዋትም እንችላለን።)
የሆነ ሆኖ ግን፣ በሕግ አግባብ (በሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 62(9) እና በአዋጅ ቁ. 359/2003) መሠረት፣ የፌደራል ጣልቃ-ገብነት የሚታዘዘው፣ በክልሎች ጥያቄና ግብዣ፣ መጠነ-ሰፊና ከክልሉ አቅም በላይ የሆኑ፦
ሀ) የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች፣
ለ) የሕግና ሥርዓት መደፍረስ፣
ሐ) ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን የሚፈታተን አደጋ ሲከሰት ብቻ ነው።
አሁን ያለው ተጨባጭ ሁኔታ የሚያሳየው፣ የፌደራል መንግሥቱ ጣልቃ መግባት እንዳለበት ሳይሆን፣ ክልሎች፣ በፌደራሉ መንግሥት “ጣልቃ በመግባት” ሥርዓት ማስፈን እንዳለባቸው ነው።(ሕጉ አይልም እንጂ!)

10. ሕገ-መንግሥታዊ ግዴታን፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥም እንኳን ሆኖ ለመወጣት መሞከር (እንደ ትግራይ ክልል)፣ የሚደገፍ፣ የሚበረታታ፣ እና የሚያስሸልም ተግባር እንጂ የሚያስተች ተግባር አይደለም።