


.. ከታየና እስክንድር ጋር የምቀርብ ተራ አናሊስት አይደለሁም።"
ጃዋር መሀመድ በራሱ ጣቢያ OMN
በቅድሚያ ተራ የሚል ራሱ - የዘቀጠ ተራ ነው።
በመቀጠል፦ የትኛውን የምርምር ሥራ አቅርበህ፤ የትኛውን የማህበራዊ ሚዲያ አንድ የረባ ስታተህ ፅፈህ ታውቅና ነው - ሌላውን ተራ ልትል የምትዳፈረው?!
*
ትላንት - ግብፆችና ሲአይኤ ጃስ እያሉ ሀገር እንድታተራምስ ይመሩህ ነበር። ዛሬ እነ ጌታቸው አሰፋና ጌታቸው ረዳ ይልኩሀል - ታስፈፅማለህ። አንተ እኮ ተራ ተላላኪ ቱቦ ነህ።
*
እኛ በማናዛቸው ሚዲያዎች - ጋዜጠኞች ቀድመን ያልሰማናቸውን - አምስት ጥያቄዎች ተጠይቀን - አንዱንም ሳንጨርስ ይነጥቁንና ወደሌላ ይሻገራሉ።
*
አንተ ግን - በራስህ ሚዲያ - ጥያቄ አዘጋጅተህ ድራማ ትሠራለህ።
ችሎታህ እኮ ቤቴን ከበቡ ብለህ ስትፅፍ ታይቷል። አንድ ዐረፍተ ነገር እንኳ አሳክተህ መፃፍ እንደማትችል ፍንትው ብሎ ተገልጿል።
ጥናትም ያጠኑልህ፤ የሚመራመሩልህ ሌሎች ናቸው። ያንተ የፖለቲካ ትንተና፦ ጥላቻ፣ መንገድ መዝጋት፣ ደም ማፋሰስ፣ ወገን ከወገን ማናከስ... ድንፋታ፣ የጎረምሳ ፉከራ፣ መንጋ ማሠማራት... "አጥንቻለሁ" - "ተናግሬ ነበር አልሰሙኝም" - "ካልኩሌተሩ እኔ ጋ ነው" ወዘተርፈ...
*
በእኔ ጀምረህ በእኔ ስትጨርስ እንጂ - የትኛውንም ታሪክና ፖለቲካ ስትተነትን ሰምተን አናውቅም። ይሄ ምክር የሚመስል አርቲ ቡርቲ... ታሪክና ፖለቲካ መሆኑ ነውን?
*
መንገድ መዝጋትና ሬሳ መቁጠር ያገነነህ - ባዶ ነህ።
*
ደግሞም እላለሁ፦ ከተራም ያነስክ ተራ - የወገንን ደም የምታፋስስ አረመኔ። አሜሪካ በገንዘብ ማጭበርበር፣ ታክስ በመሰወር የምትፈለግ ተራ ወንጀለኛ"