Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Abere
Senior Member
Posts: 12865
Joined: 18 Jul 2019, 20:52

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Abere » 10 Dec 2023, 17:08

ፋኖ ዳዴ ብሎ ጀምሮ አሁን ከአብይ አህመድ ሰራዊት ጋር ትከሻ ለትከሻ የሚለካካ ሳይሆን የአብይ ኦሮሙማ መከላከያን ቁልቁል አይቶ እየደፈቀው ነው። ስለዚህ ቀጣዩ ባለድሮን እና ተዋጊ ጄት የኢትዮጵያ አለኝታ ፋኖ መሆኑ አይቀሬ ነው። የቆየ ሰው ነጭ ጤፍ ነው ቀለቡ እንድሉ - ስቃይ እና መከራ የወለደው ጀግና የኢትዮጵያን ህዝብ ወደ ሰላም፤ፍቅር አንድነት እና የዜግነት ክብር ማማ ያወጣዋል።

Horus
Senior Member+
Posts: 34526
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Horus » 10 Dec 2023, 20:50

አበረ፤
ሁለት ነግሮች ልንገርህ፤ አንዱ ስለ ራዕይ (ሃሳብ)፣ ሌላው ስለድርድር ።

የመለኮትን ነገር ለእምነት ትተን በሰዎች አለም ውስጥ አንድ ነገር የሚወለደው ከሃሳብ ነው ። መጀመሪያ ቃል ነበረ አንዳለው ። ያ ቃል የተባለው ነገር idea ማለት ሲሆን እኛ ሃሳብ እንለዋለን፤ በጣም ስናቆላጵሰው ራዕይ (vision) እንለዋለን። ራዕይ በአይምሮአችን ውስጥ ያለ፣ የሚበራ አንድ የምንፈልገው ነገር ምስል ወይም ቅርጽ ነው ። ፋኖ ዘመናዊ የኢትዮጵያ መከላከያ የመሆን ራ ዕ ይ ባይምሮው ውስጥ አብርቶ በብልሃትና አስተውሎት እስከ ተዋጋ ድረስ ይህን ራዕዩን ቁሳዊ እውነታ ማድረጉ ምንም ጥርጥር የለውም ። ለዚህ ነው የፋኖ ኮማንደሮች እዚም እዛም ብሄራዊ ሰራዊት ስለ መሆን ሲያነሱ ልቤ የሚሞቀው ።

ደሞ ድርድርን እንመልከት፤ እንበል ያለምና ቀጠናው ኃይሎች የሆነ ያልሆነ ተጽኖ አድርገው ፋኖ ለድርድር ተቀመጠ እንበል ። ፋኖ የሚያቀርበውን የፖለቲካ ዲማንድ ወደ ጎን ትተን የሚያቀርበውን የሚሊታሪ ዲማንድ ብቻ እንመልከት ። የሚሆኑት ሁለት ነገሮች ናቸው ። የፋኖ ሰራዊት አሁን ካለው ያቢይ ሰራዊ ጋር እንዲዋሃድ ከተወሰነ ይህ ውህደት ብቻ የኢትዮጵያን መከላከያ ለንዴም ለሁሌም ይለውጠዋል ። አይ ውህደት ሳይሆን ፋኖ ትጥቁን እንደ ያዘ የፖለቲካ ሰላም ይደረግ በሚለው ከተወሰ ፋኖ ያማራን ብቻ ሳይሆን ያ4 ኪሎን ፖለቲካ ሁሉ መቆጣጠሩን ይቀጥላል ።

ከዚህ ተነስቼ ነው ደግሜ ደግሜ ፋኖ የኢትዮጵያን ፖለቲካ ከወዲሁ ለውጦታል የምለው ።



Horus
Senior Member+
Posts: 34526
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Horus » 11 Dec 2023, 03:06

የደርግ ታሪክ በወረሙማ አገዛዝ እንደ ሚደገም ጠብቁ ! ያቢይ ባለ ሟል የተባሉት 100 ብቻ እንደሆኑ ታዬ ደንዳ አረዳ ነግሮናል


Horus
Senior Member+
Posts: 34526
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Horus » 11 Dec 2023, 13:48

አቶ ታዬ ደንድአ አረዳ ሁለት ሃቆች ነግሮናል ፤

(1) አሁን ያለው የኢትዮጵያ መከላከያ ሳይሆን የአቢይ ዘብና ተላላኪ የሰፈር ፖሊስ መሆኑን (መከላከያው ፈርሷል የምንለው ለዚህ ነው)

(2) የአቢይ አገዛዝ (ሪጂም)ን አቁመው የያዙት 100 ሰዎች ብቻ ናቸው ብሏል ። (አሁን የነዚህ 100 አቢይ አሽከሮች ዝርዝዝ ለሕዝብ የማሳወቅ ኃላፊነት አለበት)



Horus
Senior Member+
Posts: 34526
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Horus » 14 Dec 2023, 15:06

መላ ያማራ ፋኖ በአንድ እዝ የሚመራ ሰራዊት መሆኑ ወደ አገር መከላከያነት የሚያደርገው ጉዞ የመጀምሪያው እርምጃ ነው !


Selam/
Senior Member
Posts: 14310
Joined: 04 Aug 2018, 13:15

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Selam/ » 14 Dec 2023, 15:39

Indeed, Taye was very articulate in this speech & he has basically spilled Abiy’s beans. PP is a group led by a bunch of thieves, whose days are numbered.
Horus wrote:
11 Dec 2023, 13:48
አቶ ታዬ ደንድአ አረዳ ሁለት ሃቆች ነግሮናል ፤

(1) አሁን ያለው የኢትዮጵያ መከላከያ ሳይሆን የአቢይ ዘብና ተላላኪ የሰፈር ፖሊስ መሆኑን (መከላከያው ፈርሷል የምንለው ለዚህ ነው)

(2) የአቢይ አገዛዝ (ሪጂም)ን አቁመው የያዙት 100 ሰዎች ብቻ ናቸው ብሏል ። (አሁን የነዚህ 100 አቢይ አሽከሮች ዝርዝዝ ለሕዝብ የማሳወቅ ኃላፊነት አለበት)



Horus
Senior Member+
Posts: 34526
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Horus » 15 Dec 2023, 21:12

ኢትዮጵያ አዲስ ብሄራዊ መከላከያ እንደ ሚያስፈልጋት ከዚህ ሌላ ምን ማስረጃ ያሰልጋል? በኦሮሙማ የ5 አመት ዘመነ መንግስት ኢትዮጵያ ብድር የማትከፍል የከሰረ፣ የኢትዮጵያ ሰራዊት በሕዝብ የተጠላ ዘራፊና እናቶች ደፋሪ ስብስብ ሆነ ! አበቃ፣ አከተመ!

Last edited by Horus on 16 Dec 2023, 01:25, edited 1 time in total.

Horus
Senior Member+
Posts: 34526
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Horus » 16 Dec 2023, 01:14

እዚህ ሃረግ ውስጥ የሚሊታሪው መሪዎች እንጀራቸው ስለሆነ ምን ግዜም ቢሆን ሚሊታሪው እንደ ድርጅት፣ as a corporation እንዲፈርስ አይፈቅዱም ብዬ ነበር ፤ ማለትም ሁሉም ነገር ከተሳካላቸውና ሁኔታዎች በነሱ መንገድ ከሄዱላቸው ። ነገር ግን ይህ አበባው የሚባል ጄኔራል ያልተማረ ሰው መሆን አለበት ።

ምን አለ መሰላችሁ? ወታደሩ ከሌለ ኢትዮጵያ ተፈርሳለች፣ ትሞታለች አለ ። ይህን ነው ካልሲካል ሚሊታሪ ኮርፖሬቲስት ቲኦሪ የሚባለው። ይህ ጄኔራል ዛሬ ላይ ጦር እያዘዘ ያለው በገበሬና መብቱን በጠየቀ የራሱ ሕዝብ ላይ ነው ። ይህን መሰል ቆሻሾች ናቸው የወታደር ጨርቃጨርቅ ለብሰው ጄኔራል የሚባሉት ።

ይህ መሰል ደደብ ነው ቋሚ ጦር ሳይኖራት 3 ሺ አመት የኖረችን አገር እኔ ከሌለሁ ኢትዮጵያ አትኖርም የሚል የታሪክ መሃይምና አድር ባይ ! እሱ ሚሊታሪውን የሚፈልገው ለኮንትራባንድና ለኑሮው መደላደያ ፣ መዝረፊያና እናቶችን መድፈሪያ እኒህን የመሳሰሉ የታሪክ ትቢያዎች ተሸክመን ነው አገር አለን የምንለው፣ ሰራዊት አለን የምንለው!

ማፈሪያዎች ።


Horus
Senior Member+
Posts: 34526
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Horus » 19 Dec 2023, 22:54

አሁን እንግዲህ የመከላከያ ሰራዊቱ ጉዳይ ብዙ ቅኔና መላምት አይሻም ። እራሱ አቢይ አህመድና የጦር ማርሻሉ በገሃድ አሳውቀውናል ። ኢትዮጵያ አሁን የወታደር ሰራዊት ያለው መከላከያ ጦር የላትም፣ ያ ፈርሷል፣ ተበትኖዋል፣ የሞተው ሞቶ የከዳው ከድቶ ፣የቀረው ወደ ትውልድ መንደሩ ተመልሷል ።

ባቢይና ብርሃኑ ጁላ መሰረት ኢትዮጵያ አሁን ያላት አርቲፊሻል መከላከያ ነው፣ ማለቴ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መከላከያ ነው ፤ ብዙ አዳዲስ ቀለም የተቀቡ ብረታ ብረቶች፣ ተተኳሽና ተኳሽ የሌላቸው ቀፎ ቆርቆሮች፣ አንድ ጥይት በ10 ሺ ዶላር የሚበሉ የ2ትና 3ስት አመት እድሜ ያላቸው ፋንሲ ማንሲ የድሮን ቴክኖሎጂ አሻንጉሊቶች ናቸው የኢትዮጵያ መከላከያ!!! ሰው አልባው ጦር ሰራዊት ይሏል! እጅ ግዙፉ የዘመናችን ድራማ!!

ልብ በሉ የአንድ ቴክኖሎጂ እድሜ ቢበዛ 2 እና 3 አመት ነው። ከዚያ በኋላ ያን የሚሽር አዲስ ይመጣል ። ከአረብ ፊውዳል መሳፍንቶች ለምኖ 2 እና 3 ሮቦቶች የሚገዛን አላዋቂ ተረኛ ከዛሬ ጀምሮ የኢትዮጵያ መከላከያ ሮቦቲክስና ሰው ሰራሽ ብረታብረት ነው ሲለን ከመገረም ሌላ ምን እንላለን ።

የዚህ ሁሉ ሰም የለበሰው ወርቅ የኢትዮጵያ ሰራዊት ለጎሳ ተረኞች ስልጣን አልሞትም ስላለ ወደ ቤቱ ተመልሷል የሚል ነው ።

ሌላ ድራማ ይዘው ብቅ እስኪሉ እንጠብቃለን


Horus
Senior Member+
Posts: 34526
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Horus » 20 Dec 2023, 16:00

የአዲስ አበባና መሃል ሸዋ ሕዝብ የቁሳኩስና የሳይኮሎጂ ዝግጅት እንዲያደርግ እየተመከረ ነው ። ይህ አገር አቀፍ ፍንዳታ ከዚህ በኋላ በማንኛውም ግዜና ቦታ እንደ ሚቀጣጠል ካለፉት የኢትዮጵያ ታሪኮች የሚታወቁ ስለሆነ። የፈረሰው የኦሮሙማ አገዛዝ በጦር ኃይል ራሱን ለመከላከል ከሞከረ እጅግ ከፍተኛ እሳተ ጎሞራ እንደ ሚቀጣጠል ጥርጥር የለውም ።


Abere
Senior Member
Posts: 12865
Joined: 18 Jul 2019, 20:52

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Abere » 20 Dec 2023, 16:32

ትግሉ ከመጨረሻው ምዕራፍ ላይ መድረሱን ያመላክታል። ፋኖ ለህዝብ እና ለዜጎች ደህንነት ያለውንም የሃላፊነት ስሜት ያንጸባርቃል።


አገራችን ዘርፈ ብዙ ችግር ውስጥ የዘፈቃት ስርዐት በአስቸኳይ ተወግዶ የኢትዮጵያን ህዝብ እና ታሪካዊ ክብር የሚመጥን መከላከያ ሰራዊት እና አገር ወዳድ መንግስት በአስቸኳይ ያስፈልጋል። እያንዳንዱ ዜጋ በአገሩ ላይ የተጋረጠውን ታሪካዊ አደጋ እና ሊያፈርሷት ያሰፈሰፉትን እኩያን መገንዘብ ታሪካዊ ግደታ ነው። በዚህ ትውልድ ዘመን መጥፎ ታሪክ እንዳይጻፍ ህሉም የዜግነት ግደታ አለበት - ይህ የጎሳ ቅራቅንቦ የችግር መቀፍቀፊያ መርዐ-ገንዳ መጣል አለበት።

Horus wrote:
20 Dec 2023, 16:00
የአዲስ አበባና መሃል ሸዋ ሕዝብ የቁሳኩስና የሳይኮሎጂ ዝግጅት እንዲያደርግ እየተመከረ ነው ። ይህ አገር አቀፍ ፍንዳታ ከዚህ በኋላ በማንኛውም ግዜና ቦታ እንደ ሚቀጣጠል ካለፉት የኢትዮጵያ ታሪኮች የሚታወቁ ስለሆነ። የፈረሰው የኦሮሙማ አገዛዝ በጦር ኃይል ራሱን ለመከላከል ከሞከረ እጅግ ከፍተኛ እሳተ ጎሞራ እንደ ሚቀጣጠል ጥርጥር የለውም ።


Horus
Senior Member+
Posts: 34526
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Horus » 20 Dec 2023, 22:44

አበረ፣
የፋኖ ጦርነት መሃል ሸዋ ሲገባ የሚሆነው እጅግ ግዙፍ ነገር ነው ። የሚሆነው የፋኖና ኦሮሙማ ታጣቂዎች ዉጊያ ብቻ አይሆንም፤ መሬት አንቀጥቃጭ ህዝባዊ ማዕበልና አመጽን ያካተተ ይሆናል ። ይህ ሲሆን ደሞ የጎሳ መተላለቅ ጭምር ይኖራል ማለትም ያዲሳባ ዙሪያ ኦነጎች ከፋኖ ጋር ካልቆሙ ወይም ገለልተኛ ካልህኑ ። ስለዚህ የሸዋ ሕዝብ በብዙ መልኩ በህቡዕ መደራትና መዛጋጀት አለበት ። ያማራ ፋኖ ባማራ ክልል ብቻ ተገድቦ እንደ ማይቀር ሳይታለም የተፈታ ነው ።

አሁን ምን አለ በል ኦሮሞቹ የሚሞክሩት ያንን ነው ። አንድ የሆነ የዉሸት ድርድር አድርገው ያማራ አመጽ ወደ መሃል ሸዋና ደቡብ ኢትዮጵያ እንዳይዘልቅ ለማስቆም በቅርብ ግዜ ድርድር ከፋኖ ጋር እንደ ሚቀመጡ ጠብቅ !

ስለዚህ የፋኖ ድርድር ጥያቄ እምብርት የሽግግር መንግስት በማድረግ ጉዳዩን በወረሙማ ያረብ አሽከሮች ቆልፎ ጦርነቱን መግፋት ነው ያለበት ፋኖ !

ethiopian
Member+
Posts: 5557
Joined: 09 Oct 2011, 21:29

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by ethiopian » 20 Dec 2023, 23:28

Horus wrote:
20 Dec 2023, 22:44
አበረ፣
የፋኖ ጦርነት መሃል ሸዋ ሲገባ የሚሆነው እጅግ ግዙፍ ነገር ነው ። የሚሆነው የፋኖና ኦሮሙማ ታጣቂዎች ዉጊያ ብቻ አይሆንም፤ መሬት አንቀጥቃጭ ህዝባዊ ማዕበልና አመጽን ያካተተ ይሆናል ። ይህ ሲሆን ደሞ የጎሳ መተላለቅ ጭምር ይኖራል ማለትም ያዲሳባ ዙሪያ ኦነጎች ከፋኖ ጋር ካልቆሙ ወይም ገለልተኛ ካልህኑ ። ስለዚህ የሸዋ ሕዝብ በብዙ መልኩ በህቡዕ መደራትና መዛጋጀት አለበት ። ያማራ ፋኖ ባማራ ክልል ብቻ ተገድቦ እንደ ማይቀር ሳይታለም የተፈታ ነው ።

አሁን ምን አለ በል ኦሮሞቹ የሚሞክሩት ያንን ነው ። አንድ የሆነ የዉሸት ድርድር አድርገው ያማራ አመጽ ወደ መሃል ሸዋና ደቡብ ኢትዮጵያ እንዳይዘልቅ ለማስቆም በቅርብ ግዜ ድርድር ከፋኖ ጋር እንደ ሚቀመጡ ጠብቅ !

ስለዚህ የፋኖ ድርድር ጥያቄ እምብርት የሽግግር መንግስት በማድረግ ጉዳዩን በወረሙማ ያረብ አሽከሮች ቆልፎ ጦርነቱን መግፋት ነው ያለበት ፋኖ !
ayeeee deha behilmu .... keep your delusional thoughts

Horus
Senior Member+
Posts: 34526
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Horus » 21 Dec 2023, 14:28

ethiopian wrote:
20 Dec 2023, 23:28
Horus wrote:
20 Dec 2023, 22:44
አበረ፣
የፋኖ ጦርነት መሃል ሸዋ ሲገባ የሚሆነው እጅግ ግዙፍ ነገር ነው ። የሚሆነው የፋኖና ኦሮሙማ ታጣቂዎች ዉጊያ ብቻ አይሆንም፤ መሬት አንቀጥቃጭ ህዝባዊ ማዕበልና አመጽን ያካተተ ይሆናል ። ይህ ሲሆን ደሞ የጎሳ መተላለቅ ጭምር ይኖራል ማለትም ያዲሳባ ዙሪያ ኦነጎች ከፋኖ ጋር ካልቆሙ ወይም ገለልተኛ ካልህኑ ። ስለዚህ የሸዋ ሕዝብ በብዙ መልኩ በህቡዕ መደራትና መዛጋጀት አለበት ። ያማራ ፋኖ ባማራ ክልል ብቻ ተገድቦ እንደ ማይቀር ሳይታለም የተፈታ ነው ።

አሁን ምን አለ በል ኦሮሞቹ የሚሞክሩት ያንን ነው ። አንድ የሆነ የዉሸት ድርድር አድርገው ያማራ አመጽ ወደ መሃል ሸዋና ደቡብ ኢትዮጵያ እንዳይዘልቅ ለማስቆም በቅርብ ግዜ ድርድር ከፋኖ ጋር እንደ ሚቀመጡ ጠብቅ !

ስለዚህ የፋኖ ድርድር ጥያቄ እምብርት የሽግግር መንግስት በማድረግ ጉዳዩን በወረሙማ ያረብ አሽከሮች ቆልፎ ጦርነቱን መግፋት ነው ያለበት ፋኖ !
ayeeee deha behilmu .... keep your delusional thoughts
ስለ
ለምን እነዚህ ዲሉዥናል ሃሳቦቼን አንድ ሁለት ብለው ላንባቢው አታሳይም? ስለ ማትችል ነው ።

Horus
Senior Member+
Posts: 34526
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Horus » 21 Dec 2023, 15:39

ማየት ማመን ነው !!! እናሳ ማነው የኢትዮጵያ መከላከያ? ፋኖ ወይስ ፒፒ? መልሱ ከታች አለ!

Horus
Senior Member+
Posts: 34526
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Horus » 23 Dec 2023, 00:00

እስቲ ዛሬ አንድ ማንም የማያነሳው ጥያቄ ላንሳ?

የአቢይ አህመድ የአማራ ጦርነት እስትራተጂክ አላማ ወይም ፐርፐዝ ምንድን ነው? ልብ በሉ ጥያቄዬ ጄኔራሎቹ ለጦርነቱ የሚጠቀሙ እስትራተጂና ታክቲክ ጉዳይ አይደለም ። ጦርነቱን እንኳ ቢያሸንፍ አቢይ አህመድ ይህን የጦርነት ድል ምን ሊያደርግበት ነው የሚያቅደው? አቢይ አህመድ ለዚህ መልስ በፍጹም የለውም፣ ሊኖረው አይችልም ።

ለምሳሌ የአማራን ሕዝብ በቅኝ ገዥነት ለመግዛት ነው?

ለምሳሌ የአማራን ክልል ከኦሮሞ ክልል ጋር ደምሮ አማራን የኦሮሞ ክልል ለማድረግ ነው?

ምንድን ነው የአቢይ ጦርነት ድህረ ድል አላማና ፕላን? መልስ የለውም ።

አንድ ያለው የደደቦች መልስ በጦርነቱ ድል ማግስት አቢይና ኦሮሙማ የአማራና ኦርቶዶክስ ኃይል በማክሰም ማንም የማይቀናቀነው የኦሮሞ ኢምፓየር እውን ለማድረግ ነው እነበል። ግ ና ይህ ስሌት የሚሰራ ነውን? ማለትም ...

ኦሮሙማ ኢምፓየር ለመሆን የተጋረጡበት መሰናክሎች አማራ ብቻ አይደለል፤ ሌሎች እጅግ ብዙ፣ እጅግ ግዙፍ ገደቦች አሉበት ። አይ ይህ የአቢይ አህመድ አልቲሜት አላማ አይደለም ከተባለ ደሞ ከላይ እንድልኩት የኦሮሙማ አማራ ላይ ጦርነት እስትራተጂክ አላማ የለውም ። የአንድ አላዋቂ መሪ ነኝ ባይ በስሜት ፈረስ መጋለብ ነው ።

አይ የኦሮሙማ ጦረኞች እስትራተጂክ አላማ ያማራ ፒፒን ስልጣን ላይ ለማኖር ነው ከተባለ ደሞ ይህ የሚሆነው በሰፋሪ የኦሮሞ ሰራዊት አማካይነት ሳይሆን፣ ፒፒ እንዲደግፍ የሚፈለገው ያማራ ሕዝብን በድሮን በመደብደብ ሳይሆን ኦሮሙማ እንዴት ከፋኖ የተሻለ ያማራ መሪ እንደ ሆነ በምሳየት ነው ። ይህ ባልሆነበት ፒፒን ስልጣን ላይ ለማኖር የሚለው በፍጹም እስትራተጂክ ግብ አይሆንም ።

በአንድ ቃል አቢይና የኦሮሞ ጓዶቹ አንድ ጥይት በ10 ሺ ዶላር እየገዙ አማራ ላይ የሚተኩሱት ምንም አይነት የመጨረሻ ግብና አላማ የሌለው የሰካራም ረብሻ ነው ። የሚያሳዝነው እንደ ቆሎ ተማሪ ከሚከተሉት 'ጄኔራል ' ተብዬዎች አንዳቸውም ይህን ጥያቄ አለማንሳታቸው ነው!

ለምንድን ነው የምንዋጋው? ብሎ የሚጠይቅ አንድ ጄኔራል እንዴት ይጠፋል !!!!

Selam/
Senior Member
Posts: 14310
Joined: 04 Aug 2018, 13:15

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Selam/ » 23 Dec 2023, 16:26

የጂኒያሙ ዓብይ አላማ ፣ የስልጣን ዘመኑን ማራዘም ብቻ ነው።
Horus wrote:
23 Dec 2023, 00:00
እስቲ ዛሬ አንድ ማንም የማያነሳው ጥያቄ ላንሳ?

የአቢይ አህመድ የአማራ ጦርነት እስትራተጂክ አላማ ወይም ፐርፐዝ ምንድን ነው? ልብ በሉ ጥያቄዬ ጄኔራሎቹ ለጦርነቱ የሚጠቀሙ እስትራተጂና ታክቲክ ጉዳይ አይደለም ። ጦርነቱን እንኳ ቢያሸንፍ አቢይ አህመድ ይህን የጦርነት ድል ምን ሊያደርግበት ነው የሚያቅደው? አቢይ አህመድ ለዚህ መልስ በፍጹም የለውም፣ ሊኖረው አይችልም ።

ለምሳሌ የአማራን ሕዝብ በቅኝ ገዥነት ለመግዛት ነው?

ለምሳሌ የአማራን ክልል ከኦሮሞ ክልል ጋር ደምሮ አማራን የኦሮሞ ክልል ለማድረግ ነው?

ምንድን ነው የአቢይ ጦርነት ድህረ ድል አላማና ፕላን? መልስ የለውም ።

አንድ ያለው የደደቦች መልስ በጦርነቱ ድል ማግስት አቢይና ኦሮሙማ የአማራና ኦርቶዶክስ ኃይል በማክሰም ማንም የማይቀናቀነው የኦሮሞ ኢምፓየር እውን ለማድረግ ነው እነበል። ግ ና ይህ ስሌት የሚሰራ ነውን? ማለትም ...

ኦሮሙማ ኢምፓየር ለመሆን የተጋረጡበት መሰናክሎች አማራ ብቻ አይደለል፤ ሌሎች እጅግ ብዙ፣ እጅግ ግዙፍ ገደቦች አሉበት ። አይ ይህ የአቢይ አህመድ አልቲሜት አላማ አይደለም ከተባለ ደሞ ከላይ እንድልኩት የኦሮሙማ አማራ ላይ ጦርነት እስትራተጂክ አላማ የለውም ። የአንድ አላዋቂ መሪ ነኝ ባይ በስሜት ፈረስ መጋለብ ነው ።

አይ የኦሮሙማ ጦረኞች እስትራተጂክ አላማ ያማራ ፒፒን ስልጣን ላይ ለማኖር ነው ከተባለ ደሞ ይህ የሚሆነው በሰፋሪ የኦሮሞ ሰራዊት አማካይነት ሳይሆን፣ ፒፒ እንዲደግፍ የሚፈለገው ያማራ ሕዝብን በድሮን በመደብደብ ሳይሆን ኦሮሙማ እንዴት ከፋኖ የተሻለ ያማራ መሪ እንደ ሆነ በምሳየት ነው ። ይህ ባልሆነበት ፒፒን ስልጣን ላይ ለማኖር የሚለው በፍጹም እስትራተጂክ ግብ አይሆንም ።

በአንድ ቃል አቢይና የኦሮሞ ጓዶቹ አንድ ጥይት በ10 ሺ ዶላር እየገዙ አማራ ላይ የሚተኩሱት ምንም አይነት የመጨረሻ ግብና አላማ የሌለው የሰካራም ረብሻ ነው ። የሚያሳዝነው እንደ ቆሎ ተማሪ ከሚከተሉት 'ጄኔራል ' ተብዬዎች አንዳቸውም ይህን ጥያቄ አለማንሳታቸው ነው!

ለምንድን ነው የምንዋጋው? ብሎ የሚጠይቅ አንድ ጄኔራል እንዴት ይጠፋል !!!!

Horus
Senior Member+
Posts: 34526
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Horus » 23 Dec 2023, 18:15

Selam/ wrote:
23 Dec 2023, 16:26
የጂኒያሙ ዓብይ አላማ ፣ የስልጣን ዘመኑን ማራዘም ብቻ ነው።
Horus wrote:
23 Dec 2023, 00:00
እስቲ ዛሬ አንድ ማንም የማያነሳው ጥያቄ ላንሳ?

የአቢይ አህመድ የአማራ ጦርነት እስትራተጂክ አላማ ወይም ፐርፐዝ ምንድን ነው? ልብ በሉ ጥያቄዬ ጄኔራሎቹ ለጦርነቱ የሚጠቀሙ እስትራተጂና ታክቲክ ጉዳይ አይደለም ። ጦርነቱን እንኳ ቢያሸንፍ አቢይ አህመድ ይህን የጦርነት ድል ምን ሊያደርግበት ነው የሚያቅደው? አቢይ አህመድ ለዚህ መልስ በፍጹም የለውም፣ ሊኖረው አይችልም ።

ለምሳሌ የአማራን ሕዝብ በቅኝ ገዥነት ለመግዛት ነው?

ለምሳሌ የአማራን ክልል ከኦሮሞ ክልል ጋር ደምሮ አማራን የኦሮሞ ክልል ለማድረግ ነው?

ምንድን ነው የአቢይ ጦርነት ድህረ ድል አላማና ፕላን? መልስ የለውም ።

አንድ ያለው የደደቦች መልስ በጦርነቱ ድል ማግስት አቢይና ኦሮሙማ የአማራና ኦርቶዶክስ ኃይል በማክሰም ማንም የማይቀናቀነው የኦሮሞ ኢምፓየር እውን ለማድረግ ነው እነበል። ግ ና ይህ ስሌት የሚሰራ ነውን? ማለትም ...

ኦሮሙማ ኢምፓየር ለመሆን የተጋረጡበት መሰናክሎች አማራ ብቻ አይደለል፤ ሌሎች እጅግ ብዙ፣ እጅግ ግዙፍ ገደቦች አሉበት ። አይ ይህ የአቢይ አህመድ አልቲሜት አላማ አይደለም ከተባለ ደሞ ከላይ እንድልኩት የኦሮሙማ አማራ ላይ ጦርነት እስትራተጂክ አላማ የለውም ። የአንድ አላዋቂ መሪ ነኝ ባይ በስሜት ፈረስ መጋለብ ነው ።

አይ የኦሮሙማ ጦረኞች እስትራተጂክ አላማ ያማራ ፒፒን ስልጣን ላይ ለማኖር ነው ከተባለ ደሞ ይህ የሚሆነው በሰፋሪ የኦሮሞ ሰራዊት አማካይነት ሳይሆን፣ ፒፒ እንዲደግፍ የሚፈለገው ያማራ ሕዝብን በድሮን በመደብደብ ሳይሆን ኦሮሙማ እንዴት ከፋኖ የተሻለ ያማራ መሪ እንደ ሆነ በምሳየት ነው ። ይህ ባልሆነበት ፒፒን ስልጣን ላይ ለማኖር የሚለው በፍጹም እስትራተጂክ ግብ አይሆንም ።

በአንድ ቃል አቢይና የኦሮሞ ጓዶቹ አንድ ጥይት በ10 ሺ ዶላር እየገዙ አማራ ላይ የሚተኩሱት ምንም አይነት የመጨረሻ ግብና አላማ የሌለው የሰካራም ረብሻ ነው ። የሚያሳዝነው እንደ ቆሎ ተማሪ ከሚከተሉት 'ጄኔራል ' ተብዬዎች አንዳቸውም ይህን ጥያቄ አለማንሳታቸው ነው!

ለምንድን ነው የምንዋጋው? ብሎ የሚጠይቅ አንድ ጄኔራል እንዴት ይጠፋል !!!!
ሰላም፣
ይህ ሁሉ የሚያደርገውማ ስልጣን ላይ ለመቆየት እንደ ሆነ ማን አጣው ? ግን ልብ በል ነገሩ ሲጀምርኮ አማራ ትክክለኛ ውክልና ይሰጠኝ አለ እንጂ መንግስት ይለወጥ አላለም ነበር። ጦርነቱ የተጀምረው አምራ አቢይ ከስልጣን ይወገድ ስላለ አልነበረም። እርግጥ ዛሬ ጥያቂው ያ የሆነው እራሱ ኦሮሙማ በሚያደርገው ጭፍ ጨፋ ከዚህ በኋላ ፋኖና አቢይ አንድ ፓርላማ የሚቀመጡ አይሆን። ከላይ እንዳልኩት አቢይን ከስልጣን ለማውረድ አማራ ብቻ ሳይሆን ሌሎችም ብዙ ኃይሎችና ፋችተሮች አሉ ። ስለዚህ ስልጣን ላይ ለመቆየት አቢይ አህመድ አማራን ምን ማድረግ ነው የሚፈልገው? ይህ ከላይ ያነሳሁት ጥያቄ ጋ ይመልሰናል ።
Last edited by Horus on 23 Dec 2023, 22:37, edited 1 time in total.

Post Reply