Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Selam/
Senior Member
Posts: 14362
Joined: 04 Aug 2018, 13:15

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Selam/ » 23 Dec 2023, 21:02

ዓላማው ስልጣኑን ለማራዘም ብቻ ስለሆነ ነው እኮ ዝብርቅርቅ ያለና በክፋትና በተንኮል የተተበተበ አስተዳደር የፈጠረው።

አስመሳይነቱ ተሟጦ ሲያልቅበት፣ በመጀመሪያ ትግራይን የስኬፕ ጎት scapegoat ምስል ኢንዲኖራት አደረገ። በመቀጠል ቢያንስ የኦሮሞን ድጋፍ እንዲያገኝ፣ በወለጋና ጋምቤላ የሚደረገው ግፍ በወያኔዎች መሰሪነት ምክንያት ነው የሚለውን ቅጥፈቱን ትቶ፣ ፒፒና ኦነግ-ሸኔን በግልጽ ተቀናጅተው የአማራን ጭፍጨፋ እንዲቀጥሉበት አደረገ። ይኸም በቂ ስለማይሆንና ገሚሱ የኦሮሞ ህዝብ መርዛማነቱን ስላወቀበት፣ የቀይ ባህርን ካርድ መዘዘ። የተወሰኑ ትግሬዎችን አስፈንጥዞ ሊሆን ይችላል እንጂ ባለማህተቡ አማራ ንቅንቅ አላለለትም። ወያኔዎችም ምርቃናቸው ከአንገት በላይ ስለሆነ፣ አመቺ ጊዜ ሲያገኙ ይበቀሉታል።

ጂኒያሙ አብይ የፋኖን ገፍቶ መምጣት ጠንቅቆ ስለሚያውቅ፣ የአማራን ህዝብ ሊያንገፈግፍ የሚችለውን ሁሉ ነገር ያደርጋል፣ ከሌሎች ብሄረሰቦች ጋርም ማንኛውም ተፅዕኖና መደማመጥ እንዳይፈጠር፣ ቅራኔዎችን መፍጠሩን ይቀጥልበታል።

ግን እድሜውን ያራዝም ይሆናል እንጂ በፋኖ ብቻም ይሁን ከሌሎች ጋራ በቅንጅት ተሽቀንጥሮ እንደሚጣል ያለቀ ጉዳይ ነው። እንደ እኔ እንደ እኔ፣ ጁላን የመሰለ ዱልዱም የካቢኔ አባል ያደረገ መንግስት፣ አንድ ሳምንትም መቆየት ባልተገባው ነበር።

Horus wrote:
23 Dec 2023, 18:15
Selam/ wrote:
23 Dec 2023, 16:26
የጂኒያሙ ዓብይ አላማ ፣ የስልጣን ዘመኑን ማራዘም ብቻ ነው።
Horus wrote:
23 Dec 2023, 00:00
እስቲ ዛሬ አንድ ማንም የማያነሳው ጥያቄ ላንሳ?

የአቢይ አህመድ የአማራ ጦርነት እስትራተጂክ አላማ ወይም ፐርፐዝ ምንድን ነው? ልብ በሉ ጥያቄዬ ጄኔራሎቹ ለጦርነቱ የሚጠቀሙ እስትራተጂና ታክቲክ ጉዳይ አይደለም ። ጦርነቱን እንኳ ቢያሸንፍ አቢይ አህመድ ይህን የጦርነት ድል ምን ሊያደርግበት ነው የሚያቅደው? አቢይ አህመድ ለዚህ መልስ በፍጹም የለውም፣ ሊኖረው አይችልም ።

ለምሳሌ የአማራን ሕዝብ በቅኝ ገዥነት ለመግዛት ነው?

ለምሳሌ የአማራን ክልል ከኦሮሞ ክልል ጋር ደምሮ አማራን የኦሮሞ ክልል ለማድረግ ነው?

ምንድን ነው የአቢይ ጦርነት ድህረ ድል አላማና ፕላን? መልስ የለውም ።

አንድ ያለው የደደቦች መልስ በጦርነቱ ድል ማግስት አቢይና ኦሮሙማ የአማራና ኦርቶዶክስ ኃይል በማክሰም ማንም የማይቀናቀነው የኦሮሞ ኢምፓየር እውን ለማድረግ ነው እነበል። ግ ና ይህ ስሌት የሚሰራ ነውን? ማለትም ...

ኦሮሙማ ኢምፓየር ለመሆን የተጋረጡበት መሰናክሎች አማራ ብቻ አይደለል፤ ሌሎች እጅግ ብዙ፣ እጅግ ግዙፍ ገደቦች አሉበት ። አይ ይህ የአቢይ አህመድ አልቲሜት አላማ አይደለም ከተባለ ደሞ ከላይ እንድልኩት የኦሮሙማ አማራ ላይ ጦርነት እስትራተጂክ አላማ የለውም ። የአንድ አላዋቂ መሪ ነኝ ባይ በስሜት ፈረስ መጋለብ ነው ።

አይ የኦሮሙማ ጦረኞች እስትራተጂክ አላማ ያማራ ፒፒን ስልጣን ላይ ለማኖር ነው ከተባለ ደሞ ይህ የሚሆነው በሰፋሪ የኦሮሞ ሰራዊት አማካይነት ሳይሆን፣ ፒፒ እንዲደግፍ የሚፈለገው ያማራ ሕዝብን በድሮን በመደብደብ ሳይሆን ኦሮሙማ እንዴት ከፋኖ የተሻለ ያማራ መሪ እንደ ሆነ በምሳየት ነው ። ይህ ባልሆነበት ፒፒን ስልጣን ላይ ለማኖር የሚለው በፍጹም እስትራተጂክ ግብ አይሆንም ።

በአንድ ቃል አቢይና የኦሮሞ ጓዶቹ አንድ ጥይት በ10 ሺ ዶላር እየገዙ አማራ ላይ የሚተኩሱት ምንም አይነት የመጨረሻ ግብና አላማ የሌለው የሰካራም ረብሻ ነው ። የሚያሳዝነው እንደ ቆሎ ተማሪ ከሚከተሉት 'ጄኔራል ' ተብዬዎች አንዳቸውም ይህን ጥያቄ አለማንሳታቸው ነው!

ለምንድን ነው የምንዋጋው? ብሎ የሚጠይቅ አንድ ጄኔራል እንዴት ይጠፋል !!!!
ሰላም፣
ይህ ሁሉ የሚያደርገውማ ስልጣን ላይ ለመቆየት እንደ ሆነ ማን አጣው ? ግን ልብ በል ነገሩ ሲጀምርኮ አማራ ትክክለኛ ውክልና ይሰጠኝ አለ እንጂ መንግስት ይለወጥ አላለም ነበር። ጦርነቱ የተጀምረው አምራ አቢይ ከስልጣን ይወገድ ስላለ አልነበረም። እርግጥ ዛሬ ጥያቂው ያ የሆነው እራሱ ኦሮሙማ በሚያደርገው ጭፍ ጨፋ ከዚህ በኋላ ፋኖና አቢይ አንድ ፓርላማ የሚቀመጡ አይሆን። ከላይ እንዳልኩት አቢይን ከስልጣን ለማውረድ አማራ ብቻ ሳይሆን ሌሎችም ብዙ ኃይሎችና ፋችተሮች አሉ ። ስለዚህ ስልጣን ላይ ለመቆየት አቢይ አህመድ አማራን ምን ማድረግ የሚፈልገው? ይህ ከላይ ያነሳሁት ጥያቄ ጋ ይመልሰናል ።
Last edited by Selam/ on 23 Dec 2023, 21:55, edited 1 time in total.

sarcasm
Senior Member
Posts: 10789
Joined: 23 Feb 2013, 20:08

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by sarcasm » 23 Dec 2023, 21:20

Inconsistency as a budge of honors

ሳይንስ፡ የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በማንኛውም ብሄር አይወሰንም By Horus
Post by Horus » 17 Dec 2023, 02:11


viewtopic.php?f=2&t=334727
Horus wrote:
17 Dec 2023, 02:11
ትግሬ + 0 = ትግሬ አልቻለም
ኦሮሞ + 0 = ኦሮሞ አልቻለም
አማራ + 0 = አማራ አልቻለም
ኦሮሞ + አማራ = ኦሮማራ አልቻለም
ኦሮሞ + ትግሬ = ትግኦሮ አይችልም
አማራ + ትግሬ =አማትግ አይችልም
ኦሮሞ + አማራ + ትግሬ =ኦሮማራትግ አይችልም
ከዛሬ እስከ አለም ፍጻሜ አንድ ጎሳ ያሻውን ያክል ቢገነታ የኢትዮጵያን እድል አይወስንም፣ አይቆጣጠርም
ያሻቸውን ያክል ጎሳዎች ቢደመሩ የኢትዮጵያን እድል አይወስኑም
የማንኛውም የጎሳ በላይነት ሂሳብ ተቃራኒ አፍራሽ የጎሳ ቀመር ይሰራለታል
ይህ ተረት አይደለም! ይህ ምኞት አይደለም
ሳይንስ ነው !

ሆረስ ነኝ


Horus
Senior Member+
Posts: 34601
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Horus » 23 Dec 2023, 23:02

ሰላም፣
"ዓላማው ስልጣኑን ለማራዘም ብቻ ስለሆነ" ብለሃል፤ በትክክል ። እኔ እዚህ ፎረም ላይ ብዙ የለጠፍኩት ነገር አለ። የማንኛውም ፖለቲከኛ ገፊና ነጂ ሞቲቬሽን (1) ስልጣን፣ (2) ገንዘብ/ሃብይ፣ (3) ክብር ፣ እና (4) ዝና/መታውቅ ናቸው ብያለሁ። ስለዚህ አይደለም አቢይን መሰል ዲሉዥናል ናርሲሲስት በዲሞክራሲ ውስጥ ያሉ ፖለቲከኞች ሁሉ ያላችው አላማ ያ ነው።

ጥያቄው ግን እንዴት ነው እነዚህን ፍላጎቶቻቸው የሚያገኙት፣ የሚያሳኩት የሚለው ነው ። ያንን ነው 'እስትራተጂክ አላማ' ያልኩት። አንተም በጨረሻው አረፍተ ነገር እንዳልክው አቢይና ቡድኑ ደደቦች ናቸው ። በኢትዮጵያ የፖለቲካ ካልቸር ውስጥ በምን መልክ ነው? በምን ዘዴ ነው? በምን መንገድ ነው ስልጣን የምይዘው? ስልጣን ላይ የምቆየው? የሃብት የክብርና ዝና ፍላጎቴን የማሟላው ለሚሉት እስትራተጂክ ጥያቄዎች የሰጡት መልስና የተከተሉት መንገድ ድድብና አላዋቂነት ነው።

አው አንተም እንዳልከው አቢይ በኃይልና በገንዘብ ፍጹም አማኝ ነው ይባላል ። ለዚህም ነው የኢሚራቲ ዶላርና የታጠቁ ዘበኞች እስካሉት ድረስ 'አልሸነፍም ' እያለ የሚያቅራራው ። ያ ሁሉ የሚያሳየው ሰውዬው የስልጣን ምኞት እንጂ ያ ስልጣንና ክብር ከኢትዮጵያ ሕዝብ እንዴት እንደ ሚገኝ ሳንቲም ኢንተለጀንስ የለውም፣ ደደብ ሰው ነው ።

ክፋትና አረመኔነቱ እስትራተጂ አልባ፣ እውቀት አልባ፣ የፖለቲካ ደንቆሮ የመሆኑ ውጤት ነው! ወዶም ሆነ ተገዶ የሚወርደው በዚያ ምክኛት ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚስማሙበት እስትራተጂ ቢኖረውማ እኛ እራሳችን ለ20 አመት ምራ እንለው አልነበረም እንዴ!
Last edited by Horus on 24 Dec 2023, 02:54, edited 1 time in total.

Horus
Senior Member+
Posts: 34601
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Horus » 23 Dec 2023, 23:15

sarcasm wrote:
23 Dec 2023, 21:20
Inconsistency as a budge of honors

ሳይንስ፡ የኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በማንኛውም ብሄር አይወሰንም By Horus
Post by Horus » 17 Dec 2023, 02:11


viewtopic.php?f=2&t=334727
Horus wrote:
17 Dec 2023, 02:11
ትግሬ + 0 = ትግሬ አልቻለም
ኦሮሞ + 0 = ኦሮሞ አልቻለም
አማራ + 0 = አማራ አልቻለም
ኦሮሞ + አማራ = ኦሮማራ አልቻለም
ኦሮሞ + ትግሬ = ትግኦሮ አይችልም
አማራ + ትግሬ =አማትግ አይችልም
ኦሮሞ + አማራ + ትግሬ =ኦሮማራትግ አይችልም
ከዛሬ እስከ አለም ፍጻሜ አንድ ጎሳ ያሻውን ያክል ቢገነታ የኢትዮጵያን እድል አይወስንም፣ አይቆጣጠርም
ያሻቸውን ያክል ጎሳዎች ቢደመሩ የኢትዮጵያን እድል አይወስኑም
የማንኛውም የጎሳ በላይነት ሂሳብ ተቃራኒ አፍራሽ የጎሳ ቀመር ይሰራለታል
ይህ ተረት አይደለም! ይህ ምኞት አይደለም
ሳይንስ ነው !

ሆረስ ነኝ

ሳርካዝም፣
መጀምሪያ የቋንቋ ስህተትክን አርም! "Inconsistency as a budge of honors" አይባልም። Badge of Honor ነው የሚባለው ። ከዛሬ ጀምሮ እንግሊዝኛ ለመጠቀም አትሞክር፣ አታውቅበትም! ሲቀጥል አየሁት የምትለው የእኔ inconsistency ምን እንደ ሆነ አንድ ሁለት ብለህ ላንባቢ አሳይ ።
Last edited by Horus on 24 Dec 2023, 02:55, edited 1 time in total.

Selam/
Senior Member
Posts: 14362
Joined: 04 Aug 2018, 13:15

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Selam/ » 23 Dec 2023, 23:26

Precisely!
Horus wrote:
23 Dec 2023, 23:02
ሰላም፣
"ዓላማው ስልጣኑን ለማራዘም ብቻ ስለሆነ" ብለሃል፤ በትክክል ። እኔ እዚህ ፎረም ላይ ብዙ የለጠፍኩት ነገር አለ። የማንኛውም ፖለቲከኛ ገፊና ነጂ ሞቲቬሽን (1) ስልጣን፣ (2) ገንዘብ/ሃብይ፣ (3) ክብር ፣ እና (4) ዝና/መታውቅ ናቸው ። ስለዚህ አይደለም አቢይን መሰል ዲሉዥናል ናርሲሲስት በዲሞክራሲ ውስጥ ያሉ ፖለቲከኞች ሁሉ ያላችው አላማ ያ ነው።

ጥያቄው እንዴት ነው እነዚህን ፍላጎቶቻቸው የሚያገኙት የሚያሳኩት የሚለው ነው ። ያንን ነው 'እስትራተጂክ አላማ' ያልኩት። አንተም በጨረሻው አረፍተ ነገር እንዳልክው አቢይና ቡድኑ ደደቦች ናቸው ። በኢትዮጵያ የፖለቲካ ካልቸር ውስጥ በምን መልክ ነው? በምን ዘዴ ነው? በምን መንገድ ነው ስልጣን የምይዘው? ስልጣን ላይ የምቆየው? የሃብት የክብርና ዝና ፍላጎቴን የማሟላው ለሚሉት እስትራተጂክ ጥያቄዎች የሰጡት መልስና የተከተሉት መንገድ ድድብና አላዋቂነት ነው።

አው አንተም እንዳልከው አቢይ በኃይልና በገንዘብ ፍጹም አማኝ ነው ይባላል ። ለዚህም ነው የኢሚራቲ ዶላርና የታጠቁ ዘበኞች እስካሉት ድረስ 'አልሸነፍም ' እያለ የሚያቅራራው ። ያ ሁሉ የሚያሳየው ሰውዬው የስልጣን ምኞት እንጂ ያ ስልጣንና ክብር ከኢትዮጵያ ሕዝብ እንዴት እንደ ሚገኝ ሳንቲም ኢንተለጀንስ የለውም፣ ደደብ ሰው ነው ።

ክፋትና አረመኔነቱ እስትራተጂ አልባ፣ እውቀት አልባ፣ የፖለቲካ ደንቆሮ የመሆኑ ውጤት ነው! ወዶም ህነ ተገዶ የሚወርደው በዚያ ምክኛት ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚስማሙበት እስትራተጂ ቢኖረውማ እኛ እራሳችን ለ20 አመት ምራ እንለው አልነበረም እንዴ!


Horus
Senior Member+
Posts: 34601
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Horus » 26 Dec 2023, 21:22

እስቲ ይህን ቃለ መጠይቅ በጥሞና አዳምጡት! ፋኖ ገና የማጥቃት ዉጊያ አልጀመረም! ያቢይ ሚሊታሪ ይህን ሁሉ መፍረስ የሚደርስበት ገና የፋኖ የማጥቃት ዘመቻ ሳይደረግበት ነው ። ዛሬ ላይ እየሆነ ያለው ያለፍላጎቱ፣ አላማ ለሌለው፣ እስትራተጂክ ግብ ለሌለው የኦሮሙማ ቅዠት መሳሪያ አሸክመው ወደ ፋኖ የሚልካቸው የርምና ደቡብ ወጣቶች መሳሪያቸውን ለፋኖ አስተላልፈው፣ አዲስ ልብስና መታወቂያ እየተሰጣቸው ወደ ቤተ ሰባቸው ይመለሳሉ !!!! አጃኢብ ማለት ነው!


Horus
Senior Member+
Posts: 34601
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Horus » 27 Dec 2023, 02:08

በዚህ ሰዓት ፋኖ አዲስ የኢትዮጵያ ብሄራዊ መከላከያ መገንባት ላይ የሚሰራ አገር አቀፍ ግብረ ኃይል ባስቸኳይ ማቋቋም አለበት ።


Horus
Senior Member+
Posts: 34601
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Horus » 29 Dec 2023, 22:33

ፋኖ ያደቀቀው ያቢይ ሰራዊት አሁን ደሞ ሸኔ በተራው እየማረከው ነው !!

Right
Member
Posts: 3787
Joined: 09 Jan 2022, 13:05

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Right » 30 Dec 2023, 08:19

The Ethiopian National Defense Force main objective is to safeguard the territorial integrity of the country.
As of today, the Sudanese Army is safeguarding a Sudanese farm settlement that has been occupied illegally. It would at least raise the concern and stationed near by.
Instead ENDF is bogged down in an ethnic civil war and village politics. Using drones and fighter jets to kill innocent citizens. Yet losing ground to Fano.

Abiye Ahmed Ali is a shame of Ethiopia. Ethiopian generals are collectively stupid following the orders of an evil dictator.

Horus
Senior Member+
Posts: 34601
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Horus » 30 Dec 2023, 12:31

Right wrote:
30 Dec 2023, 08:19
The Ethiopian National Defense Force main objective is to safeguard the territorial integrity of the country.
As of today, the Sudanese Army is safeguarding a Sudanese farm settlement that has been occupied illegally. It would at least raise the concern and stationed near by.
Instead ENDF is bogged down in an ethnic civil war and village politics. Using drones and fighter jets to kill innocent citizens. Yet losing ground to Fano.

Abiye Ahmed Ali is a shame of Ethiopia. Ethiopian generals are collectively stupid following the orders of an evil dictator.
The problem with Ethiopians is that they have little regard for time tested principles, wisdom and theories . In an ethnocracy, ethnofascism, or ethno-kleptocracy, there can not exist a national defense force. Whatever military entity that may exist would be the defense force of that ethnic ruling group or oligarch.

A great example is Sudan. RSF is a defense for a single gold mining oligarch. Abiy is is slowly becoming UAE servant oromo oligarch who is trying to rule the Ethiopian nation with his own money (UAE money) as UAE proxy in HOA.

In short, Ethiopia does not have a National Defense Force .


Horus
Senior Member+
Posts: 34601
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Horus » 03 Jan 2024, 15:23

:lol: :lol: :lol: ብርሃኑ ጁላ የዚየላ ድራማ በዩ ቲዩብ ሲከታተል ፋኖ ሰተት ብሎ ደብረ ብርሃን ግብት :lol:

Horus
Senior Member+
Posts: 34601
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Horus » 09 Jan 2024, 21:56

አቢይ አህመድ አሊ የተረፈችውን ሰራዊት ካማራ ሳያስወጣ በሱማሌ ግምባር ጦር መክፈት ይችላልን?


Horus
Senior Member+
Posts: 34601
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Horus » 10 Jan 2024, 23:51

ስርዓቱ ሞቶ ምላሱ ብቻ ነው የቀረው!!!! ፋኖ ለምን የኢትዮጵያ መከላከያ እንደ ሚሆን !!


DefendTheTruth
Senior Member
Posts: 11821
Joined: 08 Mar 2014, 16:32

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by DefendTheTruth » 11 Jan 2024, 14:04

ጉድ ነዉ፣ "ዬት ይደርሳል ተብሎ ስጠበቅ የነበረ በሬ፣ ቄራ ተገኘ" አሉ ስተርቱ።

ጉዴላዉ ጉድ ሆኖዋል፣ የአገር መከላክያ ይሆናል ያለን እንትፍ ጃዉሳ፣ አሁን ከኮሮና ጋር ተመሳስሎ ቁጭ! ይሄስ ያስብዳል፣ ስብዕና ላለዉ ሰዉ።
Please wait, video is loading...


Horus
Senior Member+
Posts: 34601
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Horus » 14 Jan 2024, 02:09

DefendTheTruth wrote:
11 Jan 2024, 14:04
ጉድ ነዉ፣ "ዬት ይደርሳል ተብሎ ስጠበቅ የነበረ በሬ፣ ቄራ ተገኘ" አሉ ስተርቱ።

ጉዴላዉ ጉድ ሆኖዋል፣ የአገር መከላክያ ይሆናል ያለን እንትፍ ጃዉሳ፣ አሁን ከኮሮና ጋር ተመሳስሎ ቁጭ! ይሄስ ያስብዳል፣ ስብዕና ላለዉ ሰዉ።
Please wait, video is loading...
እዩኝ እዩኝ ያለ ደብቁኝ ደብቁኝ ይላል እንዲሉ በእኔ ግምት ይህ ሳጥናኤል ክስረት የሚባል የከሸፈ ዲያቆን ያልታወቁ ሰዎች እንዳይጎበኙት ፈራሁለት ። ምነው ቢያርፍ ??? :lol: :lol:

Horus
Senior Member+
Posts: 34601
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ትንቢተ ሆረስ፤ ፋኖ የድህረ አቢይ ኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ይሆናል!

Post by Horus » 15 Jan 2024, 00:52

ሰሜን ሸዋ ማለት ስህተት ነው! ትክክለኛ ስማችን 'የሸዋ ፋኖ ' ነው !


Post Reply