Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Wedi
Member+
Posts: 8646
Joined: 29 Jan 2020, 21:44

Addis Abeba city Administration found out more than 100 Big buildings without "Owners"

Post by Wedi » 19 Nov 2020, 08:43

Addis Abeba city Administration found out more than 100 Big buildings without "Owners" :lol: :lol: :lol:

በአዲስ አበባ ባለቤት ያልተገኘላቸው ህንጻዎች 100 መድረሳቸውን የከተማ አስተዳደሩ ገለጸ
.
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በወቅታዊ አገራዊ ጉዳይ ላይ ከሁሉም ክፍለ ከተማ ከተውጣጡ የከተማዋ ወጣቶች ጋር በዛሬው ዕለት ውይይት አካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደገለፁት፣ በከተማዋ የሚገኙ ህንጻዎች፣ ታጥረው የሚገኙ መሬቶች እና የቀበሌ ቤቶችን በተመለከተ እየተደረገ ባለው ዳሰሳ እስካሁን 100 ህንጻዎች ባለቤት አልተገኘላቸውም።

ከዚህም በተጨማሪ ታጥሮ የተቀመጠ ከ1 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ ባለቤት ሳይገኝለት ቀርቷል።

በህገ ወጥ መንገድ የተያዙ የቀበሌ ቤቶች ላይም ማጣራት እየተደረገ መሆኑን ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናግረዋል።

በውይይቱ ላይ የተሳተፉ የከተማዋ ወጣቶች በትግራይ ክልል እየተደረገ ያለውን የሕግ ማስከበር ዘመቻ እንደሚደግፉ እና ከመከላከያ ሠራዊት ጎን መሆናቸውን ገልጸዋል።

ebc

Please wait, video is loading...

Guest1
Member
Posts: 1926
Joined: 28 Dec 2006, 01:02

Re: Addis Abeba city Administration found out more than 100 Big buildings without "Owners"

Post by Guest1 » 19 Nov 2020, 09:04

ግርግር ለሌባ ይመቻል።

Post Reply