Page 1 of 1

የመጫ ነብ እና የቱለማ ነቤ፥ የምያሰግድ የአያነ ቅዱስ መንፈስ እና የሚጠመቁት ዉሃ

Posted: 26 Jul 2026, 15:47
by Naga Tuma
አያነ የሚከበር መንፈሳዊ ነገር ነዉ። በትክክል መግለጽ ለእኔ ይከብዳል።

ዉሃን መጠመቅ በሰፊዉ የሚታወቅ ነዉ።

መጨ ያልኩኝ ምዕራብ ሸዋ ዉስጥ ነዉ።

ቱለማ ሰላሌ አከባቢ ነዉ የሚል ግምት ኣለኝ።

መጨ ዉስጥ ነብ ይከበር የነበረ አያነ መሆኑን ኣዉቃለሁ።

ነቤ ማለት ነብ ከማለት ጋር ተመሳሳይ መሆኑን ያጤንኩኝ በቅርቡ ነበር።

ነብ እና ነቤ ነብይ ከማለት ጋር ተመሳሳይ ናቸዉ።

የአሓዱ ኣምላክ ነብይ የጥንት ኢትዮጵያ ታላቅ ፈረዖ አክናተን፣ ከስደት በኋላ ፕሮፌት ሙሴ ወይም ነብዩ ሙሳ፣ መሆኑን የደረስኩበት ከሃያ ዓመታት በፊት ነዉ።

ሌላ ጥንታዊ ፈረዖ ምነስ ማለት እና ዐለም ሰገድ ማለት ያጤንኩኝ በቅርብ ነዉ።

የጥንት ኢትዮጵያ ፈረዖዎቹ አክናተን እና ምነስ፣ እንዲሁም የመጫ ነብ እና የቱለማ ነቤ ቅዱስ መንፈሶች ተቀናጅተዉ የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ዉስጥ ከሆኑ እግዝኣብሔር ዬለም ያለ ዳያብሎስ ልያከስማቸዉ ይችላል?

Re: የመጫ ነብ እና የቱለማ ነቤ፥ የምያሰግድ የአያነ ቅዱስ መንፈስ እና የሚጠመቁት ዉሃ

Posted: 07 Aug 2026, 22:29
by Naga Tuma
ኢትዮጵያ ዉስጥ እግዝኣብሔር ያያል ማለት ባህላዊ አባባል ነዉ።

በምን ግንዛቤዎች ላይ የተመሠረተ ለመሆኑ ሳይንሳዊ ጥናቶች ያረጋገጡት ነዉ ለማለት እኔ ኣጋጥሞኝ ያነበብኩኝ ሳይንሳዊ ጥናት ይህ ነዉ ማለት ኣልችልም።

ሳይንሳዊ ጥናት ባይኖርም ባህላዊ ግንዛቤዎቹ የተሳሳቱ ናቸዉ ለማለት ማረጋገጫ ኣይሆንም።

ማረጋገጫ ሊሆኑ የሚችሉትን እናጥና ቢባል ኣሳማኝ የሚሆኑት ኣንድ እና ሁለት ብቻ የሚባሉ ኣይመስለኝም።

በእያንዳንዱ ተክል ዉስጥ የፎቶስይንተሲስ ሂደት እንዳለ ሁሉ በሰዉ ልጅ ዉስጥ የመንፈስ ሂደት ይኖር ይሆን ብሎ መጠየቅ ኣስቸጋሪ ኣይመስለኝም።

ይህን የምያስጠይቀኝ የግሌ ኣስተዉሎት ነዉ።

በግሌ ኣስተዉሎት ላይ ተንተርሼ ቅዱስ መንፈስ ቀድሞ ኣይቶ ኣስቀድሞ የምያሳይ ነዉ ቢባል ስህተት ኣይመስለኝም።

የየግል ኣስተዉሎቶች ቢጠኑ ነብ ወይም ነቤ ወይም ነብይ ሲከበሩ የኖሪት ለምን እንደሆነ የጋራ ግንዛቤን ማግኘት ይቻል ይሆን?