Borkena's Post
Borkena
17h ·
#ሰበር የቴዲ አፍሮ የቅርብ ሰው በፀጥታ ሀይሎች ተወሰደ
የድምፂ ቴዎድሮስ ካሳሁን የቅርብ ጓድኛ የሆነው የሱፍ ያሲን ዛሬ ሚያዝያ 13/2018 ዓ/ም ከሰዓት በፌደራል ፖሊሶች በቁጥጥር ስር መዋሉን የቤተሰቡ አባል ተናግረዋል።
ስድስት የፌደራል ፖሊስ አባላት በድንገት ይዘውት መሄዳቸውን ነው የገለፁት።
አንጋፋው እና ተወዳጅ ድምፃዊ ቴዲ በቅርቡ የለቀቀው የኢቶሪካ አልበም ከፍተኛ ተቀባይነት በማግኘት ሁሉም ሙዚቃዎች በ24 ሰዓት ውስጥ ከአንድ ሚሊዮን በላይ እይታዎችን ማግኘት ችለዋል።
ፖሊሶቹ የሱፍ ያሲንን ከገዛ ቤቱ እና ቤተሰቡ ፊት በሀይል እየደበደቡ መውሰዳቸው፣ እርምጃው ህጋዊ ማጣራትን ሳይሆን ማስፈራራትን እና የኃይል ርምጃን ያማከለ መሆኑን ያሳያል ብለዋል።
ግለሰቡ እስካሁን የት እንደታሰረ እና በምን ወንጀል እንደተጠረጠረ በይፋ የተሰጠ መግለጫ ባይኖርም፣ የእስረኛው አያያዝ ግን በሀገሪቱ ያለውን የጸጥታ ሀይሎች የኃይል እርምጃ አሳሳቢነት ያሳየ መሆኑን ተናግረዋል።
ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ፌዴራል ፖሊስ የሱፍን በምን ጠርጥሮ እንደወሰደው አልተገለፀም።

===========================================================================================================================