Finfinne Press
''በፍቅር ጠርተው ከዳር እስከዳር
መሀል ገቡና አቆሙን ከዳር።'' ... ቴዲ አፍሮ
ይህ ግጥም ከዘፈንም በላይ ነው። በጥበብ ቃላት የተገለፀ ፣ #የብልፄን የአጥፍቶ ጠፊ የፖለቲካ መስመር የተናገረ ፣ ለስልጣን ተብሎ የተፈፀመውን ግፍ ያመላከተ ነው።
ይህ ግፍና በደል ከተፈፀመባቸው ግንባር ቀደሞቹ የኦሮሞ ልሂቃን ቀዳሚዎቹ ናቸው። ታግለው ፣ ፊት ለፊት ዋጋ ከፍለው ፣ በህይወታቸው ተወራርደው ፣ ህዝብ አታግለው ባመጡት ለውጥ ተገፍተው ከዳር እንዲቆሙ ተደርገዋል።
መገፋት ብቻ አይደለም ... በአሰቃቂ ሁኔታ የተ ገደሉ ፣ በእስር የሚማቅቁ ፣ ከሀገር እንዲሰደዱ የተደረጉ ብዙሃን ናቸው። በፍቅር ስም እየተማለ ፣ በመደመር ቀመር እየተገዘተ ... የተቀነሱ ፣ የታሰሩ ፣ የተገፉ ... ከዚህም አልፎ የህይወት መስዕዋትነት እንዲከፍሉ ተደርጓል።
አዎ ..."በፍቅር ጠርተው ከዳር እስከዳር
መሃል ገቡና አቆሙን ከዳር" .... በዚህ ጨካኝ አገዛዝ ግፍና በደል ለተፈፀመባቸው በሙሉ ይሁን