Page 1 of 1

ግምታዊ መለኮታዊ ጎህ በፍጥረት በር፥ ቁጥር 10 (ጥያቄ ቁጥር 9)

Posted: 11 Mar 2026, 18:46
by Naga Tuma
አክሱም ክርስትና ሳትቀበል በፊት ከአራት የዐለም ሃያለን መንግስታት ዉስጥ የሰየማት የነብዩ ማኒ ሃገር በዚህ ዘመን በዛን ዘመን ካልነበረ የዐለም ሃያል መንግስት ጋር ጦር መስበቅ ምን ያመለክታል?

Re: ግምታዊ መለኮታዊ ጎህ በፍጥረት በር፥ ቁጥር 10 (ጥያቄ ቁጥር 9)

Posted: 12 Mar 2026, 18:12
by Naga Tuma
ማኒቼይዝም የሚባል ከክርስትና ጋር ተፎካካሪ የነበረ ሃይማኖት የነበረ መሆኑን ለመጀመርያ ግዜ ያነበብኩኝ እ አ አ ማርች 11፣ 2026፣ ዓም ነበረ።

ይህ ክርስትናን ይፎካከር የነበረ ሃይማኖት ማሽቆልቆል የጀመረዉ ኣዉሮፓ ዉስጥ ስለ ቅድመ ክርስትና ዕዉቀት ጥናት መስፋፋት የጀመረበት ዘመን ነበር።

ስለዚህ ስለ ማኒቼይዝም ሃይማኖት መሠረት እና ምንነት ያጠኑ ኣሉ?

መለኮታዊ አሰራር በስንቶች መንገዶች የሚገለጥ ይሆን?

Re: ግምታዊ መለኮታዊ ጎህ በፍጥረት በር፥ ቁጥር 10 (ጥያቄ ቁጥር 9)

Posted: 24 Mar 2026, 21:59
by Naga Tuma
በኣባቱ በኩል የምንዛመድ ጓደኛዬ ትግርኛ ተናጋሪ እናት እኔ እንደ እናቴ የማከብራቸዉ ናቸዉ።

በወጣትነቴ ኣንድ ቀን ያለ ምንም ምክንያት ልጠይቃቸዉ ብዬ ከተማ ሄጄ ከዛን ቀን አፈሳ ኣልፌ ቤታቸዉ ስደርስ፣ ካልዘነጋሁኝ፣ ከአፈሳ እንዴት እንደኣለፍኩ የጠየቁኝ እሳቸዉ ናቸዉ።

ከኣሁን በፊት እዚህ መድረክ ላይ የኤርትራ እናቶች ፍዳ ጠንቶባቸዉ መዉለድ እርም ያላሉ ብዬ ከኣንዴ በላይ መጻፌን ኣስታዉሳለሁ።

በእኔ አስተያየት ያስተዋልኩዋቸዉ የትግራይ ሆነ የኤርትራ ክፍለ ሃገር እናቶች እግዝያር ሲሉ በሙሉ ስነልቦና ነዉ።

እነዚህ ሁሉ ለትግርኛ ተናጋሪ እናቶች ያለኝን ክብር ኣመልካች ናቸዉ ማለት የሚቻል ይመስለኛል።

ኣሁን ለትግርኛ ተናጋሪ እናቶች ያለኝ በጣም ኣጭር እና በጣም ከባድ ጥያቄ እግዝያር ባዮች እናቶች እግዝያር ኣለ ብሎ ማሰብ የኣዕምሮ መዛባት ነዉ የሚሉ ወይም ከሚሉት ጋር የዋሉ ልጆች ኣፍርተዉ እግዝያር በመለኮታዊ አሰራሩ መቅሰፍት ካወረደባቸዉ ኩነኔዉ የማን ይሆናል?

ለስንት ሺህዎች ዓመታት እግዝያር ሲል የኖረ ሕዝብ በኣንድ ትዉልድ ዕድሜ እግዝያር ኣለ ብሎ ማሰብ የኣዕምሮ መዛባት ነዉ ማለት እንዴት ይሆናል?

እግዝያር ዬለም ብሎ ዐለምን ከማግኘት እግዝያር ኣለ ብሎ ዐለምን ማጣት ይሻላል።

እ አ አ ማርች 15፣ 2026፣ ዓም

Re: ግምታዊ መለኮታዊ ጎህ በፍጥረት በር፥ ቁጥር 10 (ጥያቄ ቁጥር 9)

Posted: 25 Mar 2026, 01:18
by Naga Tuma
ስለ ሁለተኛዉ ሬይነሳንስ እዚህ መድረክ ላይ መላልሼ ጽፌኣለሁ።

ኣዲስ ኪዳን ዉስጥ ያለ ዘበትን የምያሳርም እንደሆነም መላልሼ ጽፌኣለሁ።

ያን ሁሉ ስጽፍ ስለ ፕሮፌት ማኒ እና ማኒቼይዝም የተባለ ሃይማኖት የነበረ መሆኑን ኣላዉቅም ነበር።

ይህኛዉ ግምታዊ መለኮታዊ ጎህ ጥያቄዬ ከዚህ በፊት የጠየኩትን ጥያቄዎቼን ኣጠንክሮታል።