Page 1 of 1

ግምታዊ መለኮታዊ ጎህ በፍጥረት በር፥ ቁጥር 6 (ጥያቄ ቁጥር 5)

Posted: 17 Jan 2026, 17:20
by Naga Tuma
ከአደዋ በፊት እየሱስ ተቀበልኩ ያለ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሰዉ እና ከአደዋ በኋላ እየሱስ ተቀበልኩ ያለ የኢትዮጵያ ፕሮቴስታንት ሰዉ መካከል እየሱስ ስለ ማለት ብቻ ላይ መስማማት ከጎደለ የትኛዉ የኢትዮጵያ ሰዉ ትክክል ሆነ?

እኔ እንደ ኣንድ ሰዉ ከ33 ዓመታት በላይ ስለ ሃይማኖት ኣሰላስዬ፣ ከሃያ ዓመታት በላይ ከስደት በፊት ታላቅ ፈረዖ ስለ ነበረ አክናተን፣ ከስደት በኋላ ታላቅ ፕሮፎት ሆነ ስለ ተባለዉ ሙሴ ገብቶኝ ለማስተማር የጣርኩኝ ነኝ።

ካልተሳሳትኩኝ የኢትዮጵያ ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን ከሃምሳ ዓመታት በፊት የሚከተለዉን ያለዉ እኔ ለሃያ ዓመታት ገደማ ለማስተማር ስለጣርኩኝ ነዉ።

እደ እዶ ምድር
ቃሉ የማይቀለበስ ቃሉ
ተነባቢ የአስር ምስጥር
ለካ ኣንተ ነህ!

ስለ ኣንድ ጉዳይ ከሆነ፣ መሆኑ ተጠንቶ የሚደረስበት ከሆነ፣ ሎሬቱ እኔ ጥናቱን ሳልጀምር ከብዙ ዓመታት በፊት የደረሰበት፣ እኔ የሎሬቱን ጥናት ሳላዉቅ ኣጥንቼ የደረስኩበት ነዉ ማለት ነዉ።