BBC-አስቸኳይ የቀዶ ጥገና ሕክምና ያስፈልጋቸዋል የተባሉ 16 ምርኮኞች የመንግሥት ወታደሮች በፋኖ ኃይሎች "የተናጠል እርምጃ" ተላልፈው ለቀይ መስቀል ተሰጡ
Posted: 14 Oct 2025, 18:49
መስከረም 28/2016 ዓ.ም. አስቸኳይ የቀዶ ጥገና ሕክምና ያስፈልጋቸዋል የተባሉ 16 የከባድ ጉዳት ቁስለኞችንም ወደ ሕክምና ተቋማት ማድረሱን ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ ገልጿል።
እነዚህ ቁስለኞች የመንግሥት ወታደሮች እንደሆኑ የጠቆመው ኮሚቴው፤ በፋኖ ኃይሎች "የተናጠል እርምጃ" ተላልፈው ከተሰጡት በኋላ በወልዲያ ለመንግሥት ኃይል ማድረሱን አስታውቋል።
በማግስቱ መስከረም 28፤ የቀይ መስቀል ባልደረቦች በሰሜን ወሎ በፋኖ ኃይሎች በቁጥጥር ስር የተያዙ "እስረኞችን" መጎብኘታቸውን ገልጿል።
የፋኖ ኃይሎች ከፈትነው ባሉት ዘመቻ በርካታ ወታሮችን መማረካቸውን በልሳኖቻቸው በኩል ሲያሳውቁ ሰንብተዋል።
በተለይም የሰሜን ወሎ ዞን ዋና ከተማ የሆነችውን ወልዲያን ለመያዝ ለቀናት የዘለቀ ትንቅንቅ እንደነበር ነዋሪዎች ለቢቢሲ ገልፀዋል።
ባለፈው ሳምንት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለመንግሥታቱ ድርጅት በፃፈው ደብዳቤ ወልዲያን ለመያዝ በተደረገው ውጊያ የፋኖ ኃይሎችን በመደገፍ ህወሓትን ጨምሮ ኤርትራ መሳተፏልን በመጥቀስ ከስሷል።
ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ ትናንት አርብ መስከረም 30/3018 ዓ. ም. አመሻሽ ላይ ያወጣው መግለጫ በአካባቢው የተካሄደውን ግጭት ጥልቀት እና የደረሰውን ጉዳት የሚጠቁም ነው።
https://www.bbc.com/amharic/articles/cvgjg0kk2wzo
እነዚህ ቁስለኞች የመንግሥት ወታደሮች እንደሆኑ የጠቆመው ኮሚቴው፤ በፋኖ ኃይሎች "የተናጠል እርምጃ" ተላልፈው ከተሰጡት በኋላ በወልዲያ ለመንግሥት ኃይል ማድረሱን አስታውቋል።
በማግስቱ መስከረም 28፤ የቀይ መስቀል ባልደረቦች በሰሜን ወሎ በፋኖ ኃይሎች በቁጥጥር ስር የተያዙ "እስረኞችን" መጎብኘታቸውን ገልጿል።
የፋኖ ኃይሎች ከፈትነው ባሉት ዘመቻ በርካታ ወታሮችን መማረካቸውን በልሳኖቻቸው በኩል ሲያሳውቁ ሰንብተዋል።
በተለይም የሰሜን ወሎ ዞን ዋና ከተማ የሆነችውን ወልዲያን ለመያዝ ለቀናት የዘለቀ ትንቅንቅ እንደነበር ነዋሪዎች ለቢቢሲ ገልፀዋል።
ባለፈው ሳምንት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለመንግሥታቱ ድርጅት በፃፈው ደብዳቤ ወልዲያን ለመያዝ በተደረገው ውጊያ የፋኖ ኃይሎችን በመደገፍ ህወሓትን ጨምሮ ኤርትራ መሳተፏልን በመጥቀስ ከስሷል።
ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ ትናንት አርብ መስከረም 30/3018 ዓ. ም. አመሻሽ ላይ ያወጣው መግለጫ በአካባቢው የተካሄደውን ግጭት ጥልቀት እና የደረሰውን ጉዳት የሚጠቁም ነው።
https://www.bbc.com/amharic/articles/cvgjg0kk2wzo