ሸዋ በሶዱ ህዳ ዘመን እና በዚህ ዘመን
Posted: 01 Sep 2025, 17:57
ቅጽል ስሙ ሶዱ ህዳ የተባለ ሰዉ በኢትዮጵያ ዉስጥ ለመጀመርያ ግዜ ዕጽን መትካል የጀመረ ሰዉ ነበር የሚል አፈታሪክ ሰምቻለሁ። አፈታሪኩ ትክክል ይሁን ኣይሁን ኣላረጋገጥኩም።
አፈታሪኩ የሚለዉ በዚህ ዘመን ሶዶ ጅዳ የተባለዉ ትክክለኛ ቅጽል ስሙ ሶዱ ህዳ ነበር ይላል። ቅጽል ስሙንም ያገኘዉ ስር ኣላማጅ ስለነበረ ነዉ ይላል። ህደ ማለት ስር ማለት ነዉ።
ዕጾችን እና የዱር እንስሳዎችን ኢትዮጵያ ዉስጥ ጨምሮ ማላመድ ወይም ዶመስትኬት ማድረግ የተጀመረዉ አስር ሺህዎች ዓመታት ገደማ በፊት መሆኑን ታሪክ ጸሓፊዎች ኣስቀምጠዋል።
ስለዚህ የሶዱ ህዳ አፈታሪክ ዕዉነት ከሆነ ያ ታሪካዊዉ ሰዉ ሸዋ ዉስጥ የኖረዉ አስር ሺህዎች ዓመታት ገደማ ሊሆን ይችላል?
ይህ ማለት የክርስትና ሃይማኖት ሳይፈጠር ስምንት ሺህዎች ዓመታት በፊት ማለት ነዉ።
ከሁለት አስርተ ዓመታት በፊት በአንጋፋዉ የአሜሪካ ሳይንስ መጽሔት ዉስጥ የታተመ የዲ ኤን ኤ ጥናት ሰዎች ከአዲስ አበባ ዙርያ ወደ ሌላ አለማት ፈለሱ ይላል።
ሌላ ጥልቅ የሳይንስ ጥናት መሆን የሚችል በጣም ቀላል ጥያቄ ቡዴነ መስራት የት እና መቼ ተጀመረ ነዉ። ለጥናቱ ቡዴነ የሚለዉ ቃል የተመረጠበት ምክንያት በእንግሊዘኛ ፉድ ለሚለዉ ቃል መሠረት መሆኑ ፍንጮች ስላሉ ነዉ።
ቡዴነ መስራት መጀመር ዕጽ ከማላመድ መጀመር በኋላ ብቻ ነዉ መምጣት የሚችለዉ። ቀመዲ ወይም ዊት ሳይመረት ወይም ሳይሰበሰብ በፊት ዳቦ መጋገር ሊኖር ኣይችልም።
እነዚህን ጥያቄዎች የማነሳዉ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ሸዋን ጨምሮ ኢትዮጵያ ዉስጥ ሰዎች ዕጾችን እና የዱር እንስሳዎች እያላመዱ ይኖሩ የነበረዉ ዘመን ምን ያህል ጥንታዊ እንደነበረ እራሳቸዉን ጠይቀዉ ያእራሳቸዉን መልስ እንድያገኙ ነዉ።
የዚህ የዘመን ወይም የጀበነ ጥንታዊነትን ማወቅ ከዛ በኋላ የሰዉ ልጅ ንቃተ ህሊና ምን ያህል ዳብሮ እንደነበረ መገመት እና ማጥናት ይቻላል።
ቃላትን መርጦ የመናገር እና ፊደላትን ከመፍጠር ኣልፎ ፊደላትን መርጦ መጻፍ ማለት በቀላሉ የተደረሰበት ንቃተህሊና ኣይመስለኝም። ሠ እና ሰ ተመሳሳይ ድምስ ቢኖራቸዉም የተለያየ አጠቃቀም ነበራቸዉ። ቅኔ ኣንድ ቃልን ለሰም እና ለወርቅ ይጠቀማል። መቅማቅሰ ብዙ ሳይተነትን በቂ መልዕክትን ይገልጻል።
ቤተሰብ የጉድፈቻ ልጅን የጉድፈቻ ልጅ ነህ ሳይለዉ እንደ ኣንድ ቤተሰብ አባል ኣሳድጎ ያኖራል።
በሶዱ ህዳ ዘመን ነመ ማለት እንጂ ገብረ የማለት እና የመባል ክፍፍል መኖሩን መገመት ሌላ ጥናት የምያስገዉ ርዕስ ነዉ።
ምናልባትም ሶዱ ህዳ ዕጽን ያላመደበት ዘመን ድቃላ የሚባል ቃል ሆነ አስተሳሰብ ነመ እያሉ በኖሩት ማህበረሰብ መካከል መኖሩን መገመት ያስቸግራል። በቅሎ ከፈረስ እና ከኣህያ ስለምትወለድ ድቃላ ትባላለች።
ገብረ ካሉት እና ከተባሉት የሚወለድ ሰዉ ድቃላ ይባል የነበረ መሆኑን ኣላዉቅም። የነበረ ከሆነ ፀያፍ ቃል መሆኑን ማወቅ ብዙ ትምህርት የምያስፈልግ ኣይመስለኝም።
ይህን ያህል ንቃተ ህሊና የነበረዉ ማህበረሰብ ዉስጥ ነዉ በዚህ ዘመን ፀያፍ የሆኑ የጋጠወጦች ቃላት ለሰላማዊ ሕዝብ በጋጠወጦች የሚረጩት።
ለጥፋት ወቀሳን ከሰላማዊ የዳበረ ንቃተህሊና አገላለጽ ለይቶ ማወቅም ብዙ ትምህርት የምያስፈልጉ ኣይዴለም።
እ አ አ በ1991 የኢትዮጵያ እና የኤርትራን መንግስታዊ መዋቅሮችን የተቆጣጠሩት የኤርትራዉ ኢሳያስ አፍወርቂ እና የኢትዮጵያዉ መለስ ዜናዊ እና የኦነጉ ዮሓንስ ለታ በኢትዮጵያ ላይ የማመጽ ትግሎቻቸዉን የጀመሩበት ዕድሜዎቻቸዉ በማንኛዉም መመዘኛ ምራቅ የዋጡ እና የተመራመሩ ነበሩ ማለት ኣይቻልም።
በወጣትነት ዕድሜዎቻቸዉ ዐላማ ብለዉ መነሳታቸዉ ኣይደንቀኝም።
በዚህ ዘመን እጅግ የሚገርመኝ ኣሁን በህይወት ያሉት ሆነ ታማኝ ደጋፊዎቻቸዉ ምራቅ ሳይዉጡ እና ብዙ ሳይመራመሩ የጀመሩት ትግሎቻቸዉ እንከን ዬለሽ ዐይነት ኣድርገዉ መከራከራቸዉ ነዉ።
የህዝቡን ንቃተህሊና ወደኋላ ጎትተዋል የምያስብሉ በርካታ ነገሮችን ማስተዋል ሲችሉ እንከን ዬለሽ ዐይነት ክርክሮቻቸዉን ታሪክ የምያወሳዉ እንዴት ይሆን?
አስር ሺህ ዓመታት በፊት ዕጽ ማላመድ የጀመረች ሃገር ናት የሚል የታሪክ መላምት ዕዉነት ከሆነ ከዚህ ሁሉ ዘመናት በኋላ ለመጽናት ትንገዳገዳለችን ታሪክ የምያብራራዉ እንዴት ነዉ?
ወይ መመራመር ነዉ። ወይም በተመራመሩት መመከር ነዉ።
አፈታሪኩ የሚለዉ በዚህ ዘመን ሶዶ ጅዳ የተባለዉ ትክክለኛ ቅጽል ስሙ ሶዱ ህዳ ነበር ይላል። ቅጽል ስሙንም ያገኘዉ ስር ኣላማጅ ስለነበረ ነዉ ይላል። ህደ ማለት ስር ማለት ነዉ።
ዕጾችን እና የዱር እንስሳዎችን ኢትዮጵያ ዉስጥ ጨምሮ ማላመድ ወይም ዶመስትኬት ማድረግ የተጀመረዉ አስር ሺህዎች ዓመታት ገደማ በፊት መሆኑን ታሪክ ጸሓፊዎች ኣስቀምጠዋል።
ስለዚህ የሶዱ ህዳ አፈታሪክ ዕዉነት ከሆነ ያ ታሪካዊዉ ሰዉ ሸዋ ዉስጥ የኖረዉ አስር ሺህዎች ዓመታት ገደማ ሊሆን ይችላል?
ይህ ማለት የክርስትና ሃይማኖት ሳይፈጠር ስምንት ሺህዎች ዓመታት በፊት ማለት ነዉ።
ከሁለት አስርተ ዓመታት በፊት በአንጋፋዉ የአሜሪካ ሳይንስ መጽሔት ዉስጥ የታተመ የዲ ኤን ኤ ጥናት ሰዎች ከአዲስ አበባ ዙርያ ወደ ሌላ አለማት ፈለሱ ይላል።
ሌላ ጥልቅ የሳይንስ ጥናት መሆን የሚችል በጣም ቀላል ጥያቄ ቡዴነ መስራት የት እና መቼ ተጀመረ ነዉ። ለጥናቱ ቡዴነ የሚለዉ ቃል የተመረጠበት ምክንያት በእንግሊዘኛ ፉድ ለሚለዉ ቃል መሠረት መሆኑ ፍንጮች ስላሉ ነዉ።
ቡዴነ መስራት መጀመር ዕጽ ከማላመድ መጀመር በኋላ ብቻ ነዉ መምጣት የሚችለዉ። ቀመዲ ወይም ዊት ሳይመረት ወይም ሳይሰበሰብ በፊት ዳቦ መጋገር ሊኖር ኣይችልም።
እነዚህን ጥያቄዎች የማነሳዉ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ሸዋን ጨምሮ ኢትዮጵያ ዉስጥ ሰዎች ዕጾችን እና የዱር እንስሳዎች እያላመዱ ይኖሩ የነበረዉ ዘመን ምን ያህል ጥንታዊ እንደነበረ እራሳቸዉን ጠይቀዉ ያእራሳቸዉን መልስ እንድያገኙ ነዉ።
የዚህ የዘመን ወይም የጀበነ ጥንታዊነትን ማወቅ ከዛ በኋላ የሰዉ ልጅ ንቃተ ህሊና ምን ያህል ዳብሮ እንደነበረ መገመት እና ማጥናት ይቻላል።
ቃላትን መርጦ የመናገር እና ፊደላትን ከመፍጠር ኣልፎ ፊደላትን መርጦ መጻፍ ማለት በቀላሉ የተደረሰበት ንቃተህሊና ኣይመስለኝም። ሠ እና ሰ ተመሳሳይ ድምስ ቢኖራቸዉም የተለያየ አጠቃቀም ነበራቸዉ። ቅኔ ኣንድ ቃልን ለሰም እና ለወርቅ ይጠቀማል። መቅማቅሰ ብዙ ሳይተነትን በቂ መልዕክትን ይገልጻል።
ቤተሰብ የጉድፈቻ ልጅን የጉድፈቻ ልጅ ነህ ሳይለዉ እንደ ኣንድ ቤተሰብ አባል ኣሳድጎ ያኖራል።
በሶዱ ህዳ ዘመን ነመ ማለት እንጂ ገብረ የማለት እና የመባል ክፍፍል መኖሩን መገመት ሌላ ጥናት የምያስገዉ ርዕስ ነዉ።
ምናልባትም ሶዱ ህዳ ዕጽን ያላመደበት ዘመን ድቃላ የሚባል ቃል ሆነ አስተሳሰብ ነመ እያሉ በኖሩት ማህበረሰብ መካከል መኖሩን መገመት ያስቸግራል። በቅሎ ከፈረስ እና ከኣህያ ስለምትወለድ ድቃላ ትባላለች።
ገብረ ካሉት እና ከተባሉት የሚወለድ ሰዉ ድቃላ ይባል የነበረ መሆኑን ኣላዉቅም። የነበረ ከሆነ ፀያፍ ቃል መሆኑን ማወቅ ብዙ ትምህርት የምያስፈልግ ኣይመስለኝም።
ይህን ያህል ንቃተ ህሊና የነበረዉ ማህበረሰብ ዉስጥ ነዉ በዚህ ዘመን ፀያፍ የሆኑ የጋጠወጦች ቃላት ለሰላማዊ ሕዝብ በጋጠወጦች የሚረጩት።
ለጥፋት ወቀሳን ከሰላማዊ የዳበረ ንቃተህሊና አገላለጽ ለይቶ ማወቅም ብዙ ትምህርት የምያስፈልጉ ኣይዴለም።
እ አ አ በ1991 የኢትዮጵያ እና የኤርትራን መንግስታዊ መዋቅሮችን የተቆጣጠሩት የኤርትራዉ ኢሳያስ አፍወርቂ እና የኢትዮጵያዉ መለስ ዜናዊ እና የኦነጉ ዮሓንስ ለታ በኢትዮጵያ ላይ የማመጽ ትግሎቻቸዉን የጀመሩበት ዕድሜዎቻቸዉ በማንኛዉም መመዘኛ ምራቅ የዋጡ እና የተመራመሩ ነበሩ ማለት ኣይቻልም።
በወጣትነት ዕድሜዎቻቸዉ ዐላማ ብለዉ መነሳታቸዉ ኣይደንቀኝም።
በዚህ ዘመን እጅግ የሚገርመኝ ኣሁን በህይወት ያሉት ሆነ ታማኝ ደጋፊዎቻቸዉ ምራቅ ሳይዉጡ እና ብዙ ሳይመራመሩ የጀመሩት ትግሎቻቸዉ እንከን ዬለሽ ዐይነት ኣድርገዉ መከራከራቸዉ ነዉ።
የህዝቡን ንቃተህሊና ወደኋላ ጎትተዋል የምያስብሉ በርካታ ነገሮችን ማስተዋል ሲችሉ እንከን ዬለሽ ዐይነት ክርክሮቻቸዉን ታሪክ የምያወሳዉ እንዴት ይሆን?
አስር ሺህ ዓመታት በፊት ዕጽ ማላመድ የጀመረች ሃገር ናት የሚል የታሪክ መላምት ዕዉነት ከሆነ ከዚህ ሁሉ ዘመናት በኋላ ለመጽናት ትንገዳገዳለችን ታሪክ የምያብራራዉ እንዴት ነዉ?
ወይ መመራመር ነዉ። ወይም በተመራመሩት መመከር ነዉ።