Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Za-Ilmaknun
Member
Posts: 4486
Joined: 15 Jun 2018, 17:40

BBC'የነጻ መሬት ታጣቂዎች በትግራይ ኃይሎች ላይ ጥቃት ሰነዘሩ' - የትግራይ የሰላም እና ፀጥታ ቢሮ

Post by Za-Ilmaknun » 01 Aug 2025, 11:48

የትግራይ ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ታጣቂዎች ምላዛት በተባለው አካባቢ በሰፈረው የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ኃይል ላይ ጥቃት አድርሰዋል ሲል ከሰሰ።

ቢሮው ሐሙስ ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም. አመሻሽ ላይ ባወጣው መግለጫ በአካባቢው በሚገኘው የትግራይ ታጣቂዎች ላይ በተፈጸመ ጥቃት አንድ አባል መሞቱን አስታውቋል።

ረቡዕ ሐምሌ 23/2017 ዓ.ም. በተፈጠረው ግጭት የተገደለው የትግራይ ኃይሎች አባል አንዳይ ክንደያ የተባለ መሆኑንም ገልጿል።

ትግራይ ክልል ከአፋር ጋር በሚዋሰንባቸው አካባቢዎች እንደሚንቀሳቀሱ የሚነገርላቸው እና በተለምዶ "ሓራ መሬት" (ነጻ መሬት) ተብለው የሚጠሩ ታጣቂዎች፣ ከትግራይ ኃይሎች ተነጥለው የወጡ ናቸው።

እነዚህ ታጣቂዎች በዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል የሚመራው የህወሓት ክንፍ እና ድርጅቱን የሚደግፉ የትግራይ ኃይሎች አዛዦች ከሥልጣን ለማስወገድ ወደ አፋር ክልል ሄደው መደራጀታቸውን ይናገራሉ።
በቅርቡ ራሳቸውን 'የትግራይ ሰላም ኃይል' ብለው የሰየሙት እነዚህ ታጣቂዎች በደቡብ ምሥራቅ በኩል ከትግራይ የፀጥታ ኃይሎች ጋር ግጭት ውስጥ ገብተው ነበር።

መግለጫው አክሎም 'በነጻ መሬት' ስም እያሳሳቱ ያሉት ታጣቂዎች፣ "በውጭ ኃይሎች የገንዘብ ድጋፍ የሚደረግላቸው እና በስምረት ፓርቲ እየተመሩ የትግራይ ተወላጆች እርስ በርስ እንዲጋጩ እያደረጉ ነው" በማለት ከስሷል።
ይሄንን ተከትሎ አቶ ጌታቸው ረዳ ለሊቱን በፌስቡክ ገጻቸው ላይ በሰጡት መልስ፣ ቢሮው "የትግራይን ኅልውና አደጋ ላይ የሚጥል የወንጀል መረብ አካል ነው" በማለት በገንዘብ ማጥፋት ወንጀል ከስሷል።

አቶ ጌታቸው በክልሉ ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ በእሳቸው እና በአዲሱ ፓርቲያቸው ላይ የተሰነዘረውን ክስ በተመለከተ በሰጡት ምላሽ 'ስምረት ወታደር እና ገንዘብ የለውም' በማለት በግጭቱ ውስጥ እጁ እንደሌለበት አስተባብለዋል።

https://www.bbc.com/amharic/articles/clyv7rpn40vo