የክስታኔኛ አዳረ ተነሳሳይ የፀኃይ መጥለቅና የምሽት ግዜ ዞሮ መምጣት የሚገልጽ ቃል ነው ። ዛሬ ላይ አደረ ፣ አዳሪ ፣ እንደ ምንለው ማለት ነው። አርብም ሆነ አዳረ ከጸሃይ መጥለቅ እና ከሳምንቱ የግዜ ኡደት ወይም ወረብ ጋር የተያያዘበት ምክኛት በኦሪት ክርስትና ዛሬ እሁድ ወይም አንደኛ ቀን የምንለው ቅዳሜን ነበር። እስከ አባቶቻችን ዘመን ቅዳሜ ልክ እንደ እሁድ የሚከበር ሰንበት ነበር። ስለዚህም ነው ክስታኔ ቅዳሜን ቅዳም (ቀዳሚ) ሰንበት የሚለው ።
ስለዚህ አርብ (አዳረ) የሳምንቱ መዝጊያ እና ያዲሱ ሳምንት ዋዜማ ማለት ነው/ነበር። እሁድን ክስታኔኛ ኡር ሰንበት ይለዋል ። ትርጉሙ እንደ ወረደ ዋናው ወይም የሓዲስ ኪዳን ሰንበት (ሳባዝ) ማለት ሲሆን ጥንታዊ ትርጉም የብርሃን መውጫ ቀን ማለት ነው ። ኡር ብርሃን ማለት ነው ፤ በግዕዝም በእብራይስጥም። ሰንበት (ስባዝ) የሚለው ቃል በግዕዝ ጽባህ ፣ ጽባዕ ወይም ወጣ ፣ ውጣ የምንለው ቃል ነው። ጽባህ ወንሴብሆ እጅግ ታላቅና ትልቅ ቃል ነው ።
የኬር አዳረ!