Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
sarcasm
Senior Member
Posts: 11143
Joined: 23 Feb 2013, 20:08

ምክክር ማለት ዛሬ እንደተካሄደው፤ በተቃርኖ የፖለቲካ ጎራ የተሰለፉ፤ የሚጋጩ ሕልሞችን ያነገቡ፤ በታሪክና ትርክት የማይስማሙ ማነጋነር የው። የPP ምክክር ኮምሽን በ3 ዓመት ማሳካት ያልቻለው

Post by sarcasm » 07 Jun 2025, 14:10

እንዲህ አይነቱ ነገር ለመንግስት ቄስ ሞገሴዎች [ ፋርሴ ቡላዎች ] ትልቅ እራስ ምታት ነው። ሕመማቸውን ሲያቃስቱ በየቦታው እየታዘብን ነው። ለእነርሱ ምክክር ማለት የፕሮፌሰር መስፍን አርአያ እና የጡረተኛ ጓዶቹ ወግ ነው።

በዚህም ሶስት ዓመት ሙሉ የረባ ነገር መስራት ያቃታቸው ሽማግሌዎች በተጨመረላቸው የአንድ ዓመት ጊዜ ታዐምር እንደሚሰሩ ይደሰኩራሉ። እስከአሁን የታየው የብሄራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ውጤት እና አፈፃፀም ግን በስልጠና እና ስብሰባ ጨረር እየለቀቁ የፈረንጅ ፈንድ ማሳደድ...

ምንም ሳይሰሩ በሚዲያ ጋጋታ አጃክሞ መብላትና አየር መያዝ እንዲሁም ገዥውን ፓርቲ ማድመቅ ነው። እናም ትልምና ሕልም የሌለው በሕዝቡ ያልታመነ እርባናየለሽ ግሩፕ መሆኑ በስራው ተረጋግጧል። በዚህ ላይ የሀገር ሕመም፤ የወገን ስቃይ የማይገዳቸው የመንግስት አጀንዳ አስፈፃሚዎች መሆናቸው ታይተዋል።

ማንም እንደሚረዳው ምክክር የሚያስፈልገው ልዩነትን ለማጥበብ እና ብሄራዊ መግባባትን ለመፍጠር ነው። በመሆኑም ዋንኛ የምክክሩ አካላት በተቃራኒ የፖለቲካ መስመር የተሰለፉ ሃይላት መሆን አለባቸው።

በተለይ ተቃራኒ የታሪክ አረዳድ ያላቸው፣ በሀገረ መንግስት ብያኔ የተለያየ እይታ ያላቸው፣ የሚጋጩ እና የተቃረኑ ትርክት ያነገቡ የፖለቲካ ሃይሎችን ማሳተፍ የውዴታ ግዴታ ነው። ይህ ሳይሆን ቀርቶ በመንግሥት እንደተመሠረተው አይነት የብሄራዊ የምክክር ኮሚሽን ከሆነ ከእከክልኝ ልከክልህ ያለፈ ሀገራዊ ፋይዳ አይኖረውም። ለዚህ ነው የጋሽ መስፍን አርአያ የምክክር ኮሚሽን አርአያ ላይሆን ከጅምሩ የወደቀው።

ምክክር ማለት ዛሬ እንደተካሄደው አይነት ነው። ለሀገራችንም የሚያስፈልጋት እንዲህ አይነቱ ነው። በተቃርኖ የፖለቲካ ጎራ የተሰለፉ...የሚጋጩ ሕልሞችን ያነገቡ...በታሪክ እና ትርክት የማይስማሙ ሃይላትን በአንድነት አሰባስቦ ስለ ሀገራቸው መፃኢ ዕድል እንዲነጋገሩ ማስቻል ትልቅ እርምጃ ነው።

ለሀገሪቱ የሚበጃት፣ ከጦርነት አዙሪት የሚያላቅቃት፣ የስቃይ ዘመኗን የሚያሳጥርላት...ከእሳት አበላ የሚያወጣት...ወደ ጋራ ሕልም የሚያሻግራት ይህ ነው። በመሆኑም እንዲህ አይነቱን [ምክክር] አጠናክሮ ሰፊው ሕዝብ ዘንድ ማስረፅ ያስፈልጋል። ከድፕሎማቲክ ማሕበረሰቡም አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያገኝ መስራት ይገባል።
ጥላዬ ያሚ
.
.

Affable
Member
Posts: 459
Joined: 15 Jul 2023, 13:21

Re: ምክክር ማለት ዛሬ እንደተካሄደው፤ በተቃርኖ የፖለቲካ ጎራ የተሰለፉ፤ የሚጋጩ ሕልሞችን ያነገቡ፤ በታሪክና ትርክት የማይስማሙ ማነጋነር የው። የPP ምክክር ኮምሽን በ3 ዓመት ማሳካት ያ

Post by Affable » 07 Jun 2025, 15:13

Eden, ተቃራኒ ፓርቲዊች ፣ የፓለቲካ ርእዪተአለማቸው የተለያያ ፣ ፓሊሲያቸው የማይገናኝ ለምንድነው ለምክክር የሚቀመጡት ? ምንድነው የሚመክሩት ?
ምርጫ የምናረገው መመካከር ስለማይቻል መሰሎኝ።
ሊመካከሩ የሚችሉበት ደረጃ ላይ ሊደርሱ ይችላሉ, however, የውጪ ወራሪ የመጣ እንደሆን።
ጃፓን ቻይናን ስትወር የ ቻይና ኮሚኒስት ፓርቲና ኮሚስታንግ — I might misspelled it — የጋራ ግንባር ፈጥረዋል ወራሪን ለማባረር።

Post Reply