Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Naga Tuma
Member+
Posts: 6202
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

ለናሙና ያህለ፥ ባለፉት መቶ ዐመታት አባ ገዳዎች ብያንስ አስሬ ኣልተሰባሰቡም?

Post by Naga Tuma » 07 Jun 2025, 01:29

ካልተሳሳትኩኝ በገዳ ስርዓት አባ ገዳዎች በስምንት ዐመታት ኣንድ ግዜ ይሰበሰባሉ።

እንደ ገባኝ ከሆነ የመሰብሰባቸዉ ዋና አላማ የነበረን መተዳደርያ ሕግ ወይ ለማሻሻል፣ ወይ ኣያስፈልግም ብሎ ለመጣል፣ እና ኣዲስ ሕግ ካስፈለገ ገምግሞ ለማጽደቅ ነዉ።

ይህ ስህተት ነዉ?

ስህተት ካልሆነ የቦረና ምሁራን ነን የሚሉት ብያንስ ባለፉት መቶ ዐመታት ዉስጥ የተጣሉትን፣ የተሻሻሉትን፣ እና አዲስ የወጡትን ሕግጋት ማጥናት ኣይችሉም?

ሕግጋቱ በጽሑፍ ያልተቀመጡ ከሆነ እንደ አፈ ታሪክ የሚታወቁ ኣይዴለም?

ይህን የምያስጠይቀኝ በየግዜዉ የምሰማዉ ትልቅ ወቀሳ ነዉ። ወቀሳዉ አባ ገዳ ብልት ቆራጭ ነዉ ይላል።

ይህ ትልቅ ወቀሳ ለናሙና ያህል በአፈ ታሪክም ይሁን ባለፉት መቶ ዐመታት ዉስጥ የሚታወቁ የገዳ ሕግጋት ዉስጥ መሠረት እንደሌለዉ ማስገንዘብ ኣይቻልም?

ይህን ማስገንዘብ የሚችሉ የቦረና ምሁራን ዬሉም? የቦረና ዩኒቨርዚቲ ይህን ኣጥንቶ ማስገንዘብ ኣይችልም?

እኔ የኢትዮጵያ እዴሰ ወይም ህዳሴ የምለዉ ስለ ኢትዮጵያ ጥንታዊ ቅርሶች ሁሉ ጥናት ነዉ። ስለ አክሱም ብቻ ኣይዴለም።

Naga Tuma
Member+
Posts: 6202
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

Re: ለናሙና ያህለ፥ ባለፉት መቶ ዐመታት አባ ገዳዎች ብያንስ አስሬ ኣልተሰባሰቡም?

Post by Naga Tuma » 10 Jun 2025, 17:18

የገዳ ስርዓትን በኣንድ ተግባሩ ብቻ መመዘን ይቻላል።

በየ ስምንት ዓመታት የነበረ ሕግን የሚሽር ወይም የምያሻሽል እና አዲስ ሕግን የምያጸድቅ ነዉ።

ይህ ብቻ ስልጣኔን የምያንጸባርቅ ኣይዴለም?

በእጅ ላይ ያለ ወርቅ ነሃስ ነዉ ኣሉ?

ስርዓቱን ያደነቁትን ሁለት ምሁራንን መጥቀስ በቂ ነዉ።

ኣንዱ ዶክተር ጌታቸዉ ዴሌቦ ነዉ።

ኣንድ ግዜ በአጋጣሚ ያነበብኩኝ የገዳ ስርዓት ስልጣኔ ከአክሱም ስልጣኔ በላይ ነዉ ብሎ ነበር ኣሉ። ያለዉን ቃል በቃል ባላስታዉስም አስተያየቱን ኣስታዉሳለሁ።

ሁለተኛዉ ፕሮፌሰር ዶናልድ ኤን ለቪን ነበር። እሱም የሚከተለዉን ዐይነት አስተሳሰብ ጽፏል።

The Gada system represents the most complex social organization ever devised by the human imagination (paraphrased.)

እነዚህ አስተያየቶች ብቻ ይህ የኢትዮጵያ የሆነ ታሪካዊ ቅርስ በጥልቁ ተጠንቶ ኣስፈላጊ ማሻሻያዎችን እያወጣ፣ የሃገር ሕግን ሳይጻጸር፣ ለፈለገዉ ማህበረሰብ ስራ ላይ ይዋል ማለት ከባድ ነዉ?

Misraq
Senior Member
Posts: 15552
Joined: 27 Sep 2009, 19:43
Location: Zemunda

Re: ለናሙና ያህለ፥ ባለፉት መቶ ዐመታት አባ ገዳዎች ብያንስ አስሬ ኣልተሰባሰቡም?

Post by Misraq » 10 Jun 2025, 17:56

Naga Tuna 🐟

ገዳ ሰው የሚታረድበት ቁላ የሚቆረጥበት ባዕድና ጣኦት አምልኮ ዛፍ በቂቤ ተቅምብቶ ደም ተረጭቶ ሰይጣን የሚጠራበት የክፉ መንፈስ ባህል ነው። ቀባብታችሁ ዲሞክራሲ ነው ብላችሁ ልትሸጡት ብትሞክሩም በገዳ ስርዓት የተፈጠረውን ወንጀል ምድሪቱ ራስዋ መስክራለች ትመሰክራለችም።


Post Reply