Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum

Fiyameta
Senior Member
Posts: 17439
Joined: 02 Aug 2018, 22:59

Re: የቀይ ባህር ሲቀላ መጽሐፍ ደራሲ Asham tv | አሻም ቲቪ

Post by Fiyameta » 18 May 2025, 20:52

Great videos and history. Thanks for sharing.

Dama
Member
Posts: 4461
Joined: 22 Jun 2024, 21:05

Re: የቀይ ባህር ሲቀላ መጽሐፍ ደራሲ Asham tv | አሻም ቲቪ

Post by Dama » 18 May 2025, 20:57

You were treated so good, not only by this doctor, also by all Ethiopians.
Regret you put Ethiopia through so much pain? No thank! Stay away! Or apologize sincerely and give us Assab back.

Zmeselo
Senior Member+
Posts: 35243
Joined: 30 Jul 2010, 20:43

Re: የቀይ ባህር ሲቀላ መጽሐፍ ደራሲ Asham tv | አሻም ቲቪ

Post by Zmeselo » 18 May 2025, 21:18

አረ ተዊ ባክሽ!






Dama wrote:
18 May 2025, 20:57
You were treated so good, not only by this doctor, also by all Ethiopians.
Regret you put Ethiopia through so much pain? No thank! Stay away! Or apologize sincerely and give us Assab back.



Meleket
Member
Posts: 4478
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: የቀይ ባህር ሲቀላ መጽሐፍ ደራሲ Asham tv | አሻም ቲቪ

Post by Meleket » 22 May 2025, 11:03

Meleket wrote:
30 Jan 2020, 03:08
ባንድወቅት እዚሁ መረጃ ላይ የዶልነውን የቀደምት ኤርትራዉያንን ቁምነገር ጀባ እንበላችሁ።

ከታሪክም እያጣቀስን እስቲ እንማማር!

በአጤ ኃይለሥላሴ ግዜ ኤርትራ ውስጥ የተፈጸመች አንዲት የምትነገር ጨዋታ አለች። ያኔ ያኔ ‘መደመር’ የሚባለው ፍስፍና ሳይመጣ፣ ፌደሬሽን ፈርሶ ኢትዮጵያና ኤርትራ እንኳን ተዋህደው በነበረበት ወቅት የተፈጸመች ክስተት ነች። ንጉሥ ኃይለሥላሴ ለማርያም ልዩ ፍቅር ስለነበራቸው ሁልግዜ በጥር ወር አስተርእዮ ማርያምን በምጽዋ ነበር የሚያሳልፉት ነበር አሉ። እናማ ከወቅቱ ቱባ ቱባ ባለሥልጣኖች ማለትም ከመሳፍንቶቻቸውና መኳንንቶቻቸው ጋር ሆነው በባህሩ ዳርቻ ሲንጎራደዱ፣ ነገር የጠማው በአሽሙርና ሸር የታወቀ አንድ ቀልደኛ-ቢጤ የመሀል አገር ሰው፣ በወቅቱ ከኤርትራ መኳንንት አንዱ የሆነውን፣ የቢትወደድ አስፍሃ ወልደሚካኤል ወንድምን በነገር ሊጎነትል ፈልጎ፣ ምጽዋ ባህሩ አጠገብ እየተንጎራደደ “ባህሩ የኛ ነው!” አላቸው። እኒያ ጨዋ ኤርትራዊም ሰምተው ያልሰሙ መሰሉ። ያ “ሸረኛ” ግን አሁንም በስማችው ጠርቶ እጁን ወደ ባህሩ ቀስሮ “ባህሩ የኛ ነው!” በማለት ደገመላቸው። ሰውየው አሁንም ሰምተው ያልሰሙ መስለው ችላ አሉት። ለሶስተኛ ግዜ እጁን ወደ ባህሩ እያመለከተ “ባህሩ የኛ ነው” ቢላቸው፣ ትግርኛን ብቻ ሳይሆን አማርኛንም ቅኔ የሚቀኙበት ብልሁ የቢትወደድ ወንድም ምን ቢሉት ሃሪፍ ነው። - - - “ወዳጄ፣ ያለኛ የኛ የለም!” ብለውት እርፍ። አዎን “ያለኛ የኛ የለም!”። ይህን ሁሉ በውል ይከታተሉ የነበሩት የቀልደኛውንም አጎነታተል በደንቡ ያጤኑት ንጉሡም ‘የመሀል አገሩን ሰውየ’፣ “ይህ ብልህ ልጄ እውነተኛ መልስ መለሰልህ አይደል!” አሉት ይባላል። - - - ምን ለማለት ነው። በፍቅር ሁሉ ይቻላል፣ በመከባበር ሁሉ ይቻላል፣ በወንድማማችነት ሁሉ ይቻላል፣ በመረዳዳት መንፈስ ሁሉ ይቻላል፣ ነገርግን በአሽሙር በጥላቻ በመናናቅና በቅናት መንፈስ ምንም ማድረግ አይቻልም።

ስለዚህ ኢትዮጵያውያን ሆይ የኤርትራን መሬት ስትረግጡ ጠንቀቅ በሉ፣ በስንትና ስንት ሰማዕታት ህይወት የተመሰረተች ቅድስት ሀገር ስለሆነች፣ አፋችሁ መልካም ነገር እንጂ ጉራ፣ ቀረርቶ፣ አሽሙር፣ ትዕቢት ወዘተ ወዘተ ባታስተናግዱበት ይበጃችኋል። እግራችሁ የኤርትራን መሬት ሲረግጥ፣ ይህችን ለሐቅ ሲሉ ስንትና ስንት ቅኑ ዜጎቿ የተሰውላት፣ እንደሻማ የቀለጡላት፣ የሰነከሉላት፣ የታሰሩላት፣ የተገረፉላት፣ የታረዙላት፣ የተሰደዱላትን ኤርትራንና ኤርትራውያንን አሰብ ማድረግ ይጠበቅባችኋል። ይህን ካደረጋችሁ የኤርትራንና ኤርትራውያንን ፍቅር ያለ ገደብ ታገኛላችሁ። እኛ ኤርትራውያን ጠቅላይ አብይን የምናከብራቸው፣ በዚች እጅግ አጭር የስልጣን ግዚያቸው፣ በርካታ እስረኞችን ሞትም የተፈረደባቸውን እንደ አቶ አንዳርጋቸው አይነቶችን ሰዎች ጭምር ስለፈቱ፣ ተፎካካሪ እንጂ ተቃዋሚ የሚባል ነገር የለም የሚል አመለካከትን ስላስተዋወቁ፣ በውጪ ሃገር የሚኖሩ ፖለቲከኞችንና የመገናኛ ብዙሓንን ወደ ሃገረ ውስጥ ገብተው ገንቢ ሚና እንዲያበረከቱ ጥሪ ስላደረጉ፣ በአካልም ሄደው የልብ ትርታቸውን ስላደመጡ፣ በቀጠናችን ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ይቅርታን በተግባር ስላስተማሩ፣ እንደመር እንፋቀር ስላሉ፣ የህዝባቸውን የልብ ትርታ ለማድመጥ ስለሚጥሩ፣ የተጣሉና የተኳረፉ የሃይማኖት አባቶችን ሳይቀር ስላግባቡና ስላስታረቁ፣ አንደበታቸው በሳልና ርቱዕ ስለሆነ፣ ትሑት ስለሆኑ፣ እውነትን ስለሚወዱ፣ የሰው ገንዘብ ስለማይመኙ ወዘተ ብቻ አይደለም፣ ሰማእታቶቻችንንም ስላከበሩ ነው። ኤርትራ፣ ሃገረ - ሰማእታት ናትና!

ያለኛ የኛ የለም! :mrgreen:

ፈጣሪ ኤርትራንና ኤርትራውያንን ይባርክ!
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያውያንን ይባርክ!


https://mereja.com/forum/viewtopic.php? ... 24#p818624

Post Reply