BBC:- ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከፖለቲካ ፓርቲነት በኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ተሰረዘ!
Posted: 14 May 2025, 12:03
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት (ህወሓት) ከገንቦት 5/2017 ዓ.ም. ጀምሮ ከፖለቲካ ፓርቲነት መሰረዙን አስታወቀ።
ቦርዱ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው ህወሓት ከየካቲት 5/2017 ዓ.ም. ጀምሮ ዕግድ በመጣል ህወሓት የሚጠበቅበትን የእርምት እርምጃ እንዲወስድ የሰጠው ጊዜ በመጠናቀቁ በድርጅቱ ላይ የመሰረዝ ውሳኔ አሳልፏል።
ከአራት ዓመት በፊት በትግራይ ውስጥ ከተቀሰቀሰው ጦርነት ጋር በተያያዘ በአገሪቱ ምክር ቤት በሽብር ቡድንነት ተፈርጆ የነበረው ህወሓት፣ በኃይል እንቅስቃሴ ውስጥ በመሳተፉ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተሰርዞ እንደነበር ይታወሳል።
ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ በአመጻ ድርጊት በመሳተፉ የተነሳ በአዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀፍ 98 መሠት ከፖለቲካፓርቲነት መሠረዙን ምርጫ ቦርድ ባወጣው መግለጫ ላይ አስታውሷል።
ነገር ግን በፌደራል መንግሥቱ እና በትግራይ ታጣቂዎች መካከል ለሁለት ዓመት ሲካሄድ የቆየው ጦርነት በፕሪቶሪያ ስምምነት መቋጨቱን ተከትሎ የኢትዮጵያ የምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅን ለማሻሻል በወጣው አዋጅ አማካይነት ህወሓት በልዩ ሁኔታ ለመመዝገብ ችሎ ነበር።
https://www.bbc.com/amharic/articles/c5yeglldnqyo
ቦርዱ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው ህወሓት ከየካቲት 5/2017 ዓ.ም. ጀምሮ ዕግድ በመጣል ህወሓት የሚጠበቅበትን የእርምት እርምጃ እንዲወስድ የሰጠው ጊዜ በመጠናቀቁ በድርጅቱ ላይ የመሰረዝ ውሳኔ አሳልፏል።
ከአራት ዓመት በፊት በትግራይ ውስጥ ከተቀሰቀሰው ጦርነት ጋር በተያያዘ በአገሪቱ ምክር ቤት በሽብር ቡድንነት ተፈርጆ የነበረው ህወሓት፣ በኃይል እንቅስቃሴ ውስጥ በመሳተፉ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተሰርዞ እንደነበር ይታወሳል።
ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ በአመጻ ድርጊት በመሳተፉ የተነሳ በአዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀፍ 98 መሠት ከፖለቲካፓርቲነት መሠረዙን ምርጫ ቦርድ ባወጣው መግለጫ ላይ አስታውሷል።
ነገር ግን በፌደራል መንግሥቱ እና በትግራይ ታጣቂዎች መካከል ለሁለት ዓመት ሲካሄድ የቆየው ጦርነት በፕሪቶሪያ ስምምነት መቋጨቱን ተከትሎ የኢትዮጵያ የምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅን ለማሻሻል በወጣው አዋጅ አማካይነት ህወሓት በልዩ ሁኔታ ለመመዝገብ ችሎ ነበር።
https://www.bbc.com/amharic/articles/c5yeglldnqyo