Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
MINILIK SALSAWI
Member+
Posts: 9984
Joined: 24 Aug 2012, 12:02
Contact:

በትግራይ የፖለቲካ ትኩሳት፤ የኤርትራ ሚና ምንድነው?

Post by MINILIK SALSAWI » 13 Mar 2025, 13:25

በትግራይ የፖለቲካ ትኩሳት፤ የኤርትራ ሚና ምንድነው?

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ በአዲስ አበባ በሰጡት መግለጫ፤ “በትግራይ ትርምስ እናተርፋለን ከሚሉት ወገኖች አንዱ የኤርትራ መንግስት ነው” ብለዋል። በትግራይ ያሉ የተወሰኑ ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ አመራሮች ከሻዕቢያ ጋር “ግንኙነት አላቸው” ሲሉም ወንጅለዋል።

ቀደም ባሉት ጊዜያት እርሳቸውም ቢሆኑ “ከኤርትራ መንግስት ጋር ሰላም መፍጠር አለብን” በሚል እምነት “የተወሰነ እንቅስቃሴ” ያደርጉ እንደነበር አቶ ጌታቸው በዛሬው መግለጫቸው አምነዋል። በትግራይ ያሉ የተወሰኑ ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ አመራሮች አሁን የፈጠሩት ግንኙነት ግን የክልሉን “ህልውና” “አደጋ ላይ የሚጥል” እንደሆነ አስገንዝበዋል።

አቶ ጌታቸው “ጥቂት” ግን “አደጋ መፍጠር የሚችሉ” ሲሉ የጠሯቸው አመራሮች የፈጠሩት ግንኙነት ችግር የሚያስከትለው፤ “ለትግራይ ህዝብ ማር በማዝነብ ከሚታወቁ ሰዎች ጋር ስላልሆነ ነው” ብለዋል። ከኤርትራ ጋር እየተደረገ ያለው ይህ ግንኙነት፤ የትግራይን ፖለቲካ “ከማመስ አንጻር አስተዋጽኦ የለውም ማለት አይቻልም” ሲሉም ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።

“የኤርትራ መንግስት ሰዎች ፍላጎት፤ የኢትዮጵያ መንግስት ‘ኤርትራን ይወራል’ ብለው በሚሰጉበት ሰዓት፤ ትግራይን ማቀዝቀዣ buffer እንዲሆን ማድረግ ነው። ጠንከር ያለ አጋጣሚ ተፈጥሯል ብለው ካመኑ ደግሞ፤ ከእኛ ሰዎች ጋር ሆነው እንደገና ወደ አዲስ አበባ ጉዞ ማድረግ የሚቻልበት ዕድል ካለ ማመተርም ሊሆን ይችላል” ሲሉም አቶ ጌታቸው ተደምጠዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

🔴የኤርትራን ሚና በተመለከተ አቶ ጌታቸው የሰጡትን ማብራሪያ ለመመልከት ➡️



Zmeselo
Senior Member+
Posts: 35028
Joined: 30 Jul 2010, 20:43

Re: በትግራይ የፖለቲካ ትኩሳት፤ የኤርትራ ሚና ምንድነው?

Post by Zmeselo » 13 Mar 2025, 13:50

የኢትዮጵያ ልሂቃን፡ የሆነ ችግር ሲደርሳቸዉ፡ ኤርትራን መክሰስና እንደ ገንሸል የመጠቀም ሙከራ የታወቀ ኣመላቸዉ ነዉ።
MINILIK SALSAWI wrote:
13 Mar 2025, 13:25
በትግራይ የፖለቲካ ትኩሳት፤ የኤርትራ ሚና ምንድነው?

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ በአዲስ አበባ በሰጡት መግለጫ፤ “በትግራይ ትርምስ እናተርፋለን ከሚሉት ወገኖች አንዱ የኤርትራ መንግስት ነው” ብለዋል። በትግራይ ያሉ የተወሰኑ ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ አመራሮች ከሻዕቢያ ጋር “ግንኙነት አላቸው” ሲሉም ወንጅለዋል።

ቀደም ባሉት ጊዜያት እርሳቸውም ቢሆኑ “ከኤርትራ መንግስት ጋር ሰላም መፍጠር አለብን” በሚል እምነት “የተወሰነ እንቅስቃሴ” ያደርጉ እንደነበር አቶ ጌታቸው በዛሬው መግለጫቸው አምነዋል። በትግራይ ያሉ የተወሰኑ ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ አመራሮች አሁን የፈጠሩት ግንኙነት ግን የክልሉን “ህልውና” “አደጋ ላይ የሚጥል” እንደሆነ አስገንዝበዋል።

አቶ ጌታቸው “ጥቂት” ግን “አደጋ መፍጠር የሚችሉ” ሲሉ የጠሯቸው አመራሮች የፈጠሩት ግንኙነት ችግር የሚያስከትለው፤ “ለትግራይ ህዝብ ማር በማዝነብ ከሚታወቁ ሰዎች ጋር ስላልሆነ ነው” ብለዋል። ከኤርትራ ጋር እየተደረገ ያለው ይህ ግንኙነት፤ የትግራይን ፖለቲካ “ከማመስ አንጻር አስተዋጽኦ የለውም ማለት አይቻልም” ሲሉም ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።

“የኤርትራ መንግስት ሰዎች ፍላጎት፤ የኢትዮጵያ መንግስት ‘ኤርትራን ይወራል’ ብለው በሚሰጉበት ሰዓት፤ ትግራይን ማቀዝቀዣ buffer እንዲሆን ማድረግ ነው። ጠንከር ያለ አጋጣሚ ተፈጥሯል ብለው ካመኑ ደግሞ፤ ከእኛ ሰዎች ጋር ሆነው እንደገና ወደ አዲስ አበባ ጉዞ ማድረግ የሚቻልበት ዕድል ካለ ማመተርም ሊሆን ይችላል” ሲሉም አቶ ጌታቸው ተደምጠዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

🔴የኤርትራን ሚና በተመለከተ አቶ ጌታቸው የሰጡትን ማብራሪያ ለመመልከት ➡️


MINILIK SALSAWI
Member+
Posts: 9984
Joined: 24 Aug 2012, 12:02
Contact:

Re: በትግራይ የፖለቲካ ትኩሳት፤ የኤርትራ ሚና ምንድነው?

Post by MINILIK SALSAWI » 14 Mar 2025, 06:55

" ከኤርትራ መንግስት ግንኙት አላችሁ የሚል ወሬ በሬ ወለደ ውሸት ነው " - ጉባኤ ያካሄደው ህወሓት 

➡️ " የኤርትራ መንግስት የያዘው ትግራይ መሬት የለም " - የኤርትራ ከፍተኛ ባለስልጣን 

ጉባኤ ያካሄደ ህወሓት ምክትል ሊቀ-መንበር ኣማኒኤል ኣሰፋ " ' በትግራይ መፈንቅለ መንግስት ተካሂደዋል ' የሚባለው ፍፁም ውሸት ነው ፤ ህወሓት በጊዚያዊ አስተዳደሩ ያለውን የስልጣን ድርሻ ከማስተካከል የዘለለ አንዳች የወሰደው እርምጃ የለም " አሉ።

" ህዝቡን በተዘባ ወሬ ወደ አላስፈላጊ ውዥንብር በማስገባት መሬት ላይ በሌለ ግጭት ውጥረት ውስጥ ማስገባት ሃላፊነት ከሚሰማው ፓለቲከኛ የሚጠበቅ አይደለም " ሲሉም ተናግረዋል።

" ህዝቡ የሚያሰጋ ነገር በሌለበት ሁኔታ ገንዘብ ከባንክ ለማወጣትና አስቤዛ ለመገዛት መሯሯጥ አይገባውም " ሲሉ ገልጸዋል።

በትግራይ ክልል ባለው ሁኔታ ነዋሪዎች ጦርነት ይቀሰቀሳል በሚል በስፋት ከባንክ ገንዘብ እያወጡ አስቤዛም በስፋት እየገዙ ይገኛሉ።

አቶ አማኒኤል ፤ " ህወሓት በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት ለፌደራሉ መንግስት የሰጠው እውቅናን በማጠናከር በመመካከር መስራቱን ይቀጥላል " ያሉ ሲሆን " ፓርቲው ባነሳቸው የጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ምትክ ከፌደራል መንግስት በመተማመን አዲስ ፕሬዜዳንት ይመርጣል " ሲሉ ተናግረዋል።

" ህወሓት የትግራይ ሰራዊት በማያሳምን መንገድ ለመበታተን የሚደረግ ሴራ እንጂ DDR መተገበርን አይቃወምም " ያሉት ምክትል ሊቀ-መንበሩ ፤ " ፕሬዜዳንት ነበር " ሲሉ የጠሩዋቸው አቶ ጌታቸው ረዳ በከፍተኛ የሰራዊት አመራሮች የወሰዱት እርምጃ " በሌለ ስልጣን የተደረገና ተቀባይነት  የሌለው " ሲሉ አጣጥለውታል።

አቶ አማኒኤል የተወሰኑ የህወሓት አንጃዎች ከሻዕቢያ ጋር  ግንኙነት አላቸው በሚባለው ጉዳይ " ከኤርትራ መንግስት ጋር ግንኙት አላችሁ የሚል ወሬ በሬ ወለደ ውሸት ነው " ሲሉ መልሰዋል።

" ከኤርትራ መንግስት ከኢትዮጵያ መንግስት እውቅና ውጪ የሚካሄድ ግንኙነት የለም "  ሲሉም አክለዋል።

በኤርትራ ወታደሮች ቁጥጥር ስር ስለሚገኙ የኢትዮጵያ የትግራይ ክልል ቦታዎች ምንም ያሉት ነገር የለም።

በተያያዘ " የኤርትራ መንግስት የያዘው የትግራይ መሬት የለም " ሲሉ አንድ የኤርትራ ከፍተኛ ባለስልጣን ፅፈዋል። 

ባለስልጠኑ የማነ ገ/መስቀል  " ይድረስ ለግጭት ጠማቂዎች " በሚል በX ገፃቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ " የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መተግበርና አለመተግበር የኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ እንጂ ኤርትራ አይመለከትም " ብለዋል።  

" የህወሓት መከፋፈል ኤርትራን አይመለከትም " ያሉት ባለስልጣኑ " የትግራይ ህዝብ የውስጥ ሰላም እንዲበጠበጥ ኤርትራ ምንም ዓይነት ፍላጎት የላትም " ብለዋል።

" የተለያየ የፓለቲካ እሳቤ ያላቸው የኢትዮጵያ ፓለቲከኞች የቀይ ባሀርን አጀንዳ እንደ አዲስ በማቀጣጠል የአፍሪካ ቀንድን ለሌላ ተጨማሪ ውጥረት ከማስገባት እንዲቆጠቡ " በማለትም ባለስልጣኑ በX ገፃቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ አሳስበዋል።

ባለስልጣኑ ይህን ይበሉ እንጂ  የኤርትራ ሰራዊት በኢትዮጵያ የትግራይ የደንበር አከባቢ በርካታ ቦታዎች ይዞ ይገኛል።

በርካታ በትግራይ ምስራቃዊ ፣ ማእከላዊ ሰሜን ምዕራብ ዞን የሚገኙ ቀበሌ ገበሬ ማህበራት በኤርትራ ወታደሮች ቁጥጥር ስር እንደሚገኙ ደጋግሞ የዘገበው ቲክቫህ  ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አሁንም በመሬት ላይ የተለወጠ አዲስ ነገር እንደሌለ የአከባቢው ነዋሪዎች በመጠየቅ አረጋግጧል።

Fiyameta
Senior Member
Posts: 17062
Joined: 02 Aug 2018, 22:59

Re: በትግራይ የፖለቲካ ትኩሳት፤ የኤርትራ ሚና ምንድነው?

Post by Fiyameta » 14 Mar 2025, 07:29

Our role in Tigray is filling the void left by USAID. :P

Post Reply