የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሜጀር ጄኔራል አበበ ተክለ ሃይማኖት (ጆቤ)፣ የኢትዮጵያና የኤርትራ ግንኙነት መጀመሪያውንም ያልተቀደሰ ግንኙነት እንደነበር ጠቁመው፣ ወደ ግጭት ሊያመሩ እንደሚችሉ የሚያመላክቱ ፍንጮች እንዳሉ ተናገሩ፡፡
ኢትዮጵያ የወደብ ተጠቃሚ መሆን የምትችልባቸውን ሁኔታዎች በተመለከተ ከሦስት ዓመታት በፊት የሠሩትን ጥናታዊ ጽሑፍ አስታውሰው፣ ጥያቄው ግን በጉልበት መመለስ የለበትም ብለዋል፡፡ በአገሮቹ መካከል ጦርነት ቢቀሰቀስ አቅጣጫው ምን ይሆናል የሚለው ጉዳይ የሚታወቀው የጦርነቱ ዓላማ ሲታወቅ እንደሆነ ጠቅሰው፣ ‹‹ጦርነቱ አንድም አሰብን መያዝ፣ ሁለተኛው ደግሞ ሻዕቢያን ማስወገድ ሊሆን ይችላል፤›› ሲሉ አስረድተዋል፡፡
የጦርነቱ ዓላማ አሰብን መያዝ ከሆነ የሁለቱን አገሮች የመሣሪያና የቴክኖሎጂ አቅም መገምገም እንደሚገባ ጠቅሰው፣ የሻዕቢያን መንግሥት የመጣል ዓላማ ካለ ደግሞ፣ የኤርትራ ዕጣ ፈንታ የሚያሳስባቸው እንደ አሜሪካ ያሉ አገሮች ጣልቃ ገብነት የሚጠበቅ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
‹‹እነ አሜሪካ፣ ቻይናና ሩሲያ ጉዳዩን እንዴት ያዩታል? ግብፅስ ለማን ትወግናለች? የሚለውም ሌላኛው ጉዳይ ነው፡፡ ኢትዮጵያ አሰብን ልያዝ ብትል፣ የተባበሩት ዓረብ ኢምሬትስ ቢደግፏት፣ ሳዑዲ ዓረቢያ ግን ደስተኛ ላትሆን ትችላለች፡፡ እንዲህ ዓይነት ቀውስ ግብፅንም መጋበዙ አይቀርም፡፡ የሶማሊያና የሶማሌላንድን ፍላጎት የቱርክ አሸማጋይ ሆኖ በቀጣናው ውስጥ መገኘት፣ እንዲሁም የዶናልድ ትራምፕን ወደ ሥልጣን መምጣትን ማመዛዘን ያስፈልጋል፡፡ የቀጣናው አሠላለፍ ይቀየር ቢባል እንኳን፣ አሠላለፉን በቀይ ባህር ብቻ መቀየር አይቻልም፡፡ አሰብን መያዝ የኢትዮጵያ ጉዳይ ብቻ እንዳልሆነ መገንዘብ ይገባል፤›› ሲሉ አብራርተዋል፡፡
ከ28 ዓመታት በፊት በተካሄደው የኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ወቅት ሻዕቢያን የመደምሰስ አቅም የነበረ ቢሆንም ይህ አለመደረጉ ትልቅ ስህተት እንደነበር የገለጹት የቀድሞው የአየር ኃይል ዋና አዛዥ፣ ከዚያ በኋላ በነበሩት 18 ዓመታት የተሠራው ጠላትን በዝምታ የማቆየት ትልቅ ስህተት ከባድ ዋጋ ማስከፈሉን ተናግረዋል፡፡ በተለይም በሰሜኑ ጦርነት ወቅት የትግራይ ሕዝብ ዋጋ እንዲከፍል ምክንያት ሆኗል ብለው፣ አሁንም ጦርነት ከተቀሰቀሰ የትግራይ ክልል የጦርነት ዓውድማ ሊሆን የሚችልበት ዕድል ሰፊ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ የፌዴራሉ መንግሥት ሠራዊት ቲዲኤፍ ከሚባለው የክልሉ ሠራዊት ጋር ሳይስማማ ወደ ትግራይ መግባት ይችላል ወይ? የሚለው ጉዳይ አጠያያቂ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ከ28 ዓመታት በፊት ‹‹ኢትዮጵያ በፌደራሊዝም ሥርዓት ተሳስራለች፡፡ የአየር ኃይልም የላትም በሚል ሻዕቢያ ወረራ ፈጽሟል፤›› ያሉት ሜጀር ጄኔራል አበበ፣ በወቅቱ የመከላከያ ሠራዊቱ የማዕከላዊ ኮማንድ አባል እንደነበሩና ሻዕቢያን አስመራ ድረስ ገብቶ የመደምሰስ ውሳኔ ላይ ተደርሶ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ ይሁንና በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ውሳኔ መሠረት፣ ‹‹ኤርትራን ማዳከም በቂ ነው›› ተብሎ እንዲመለሱ መታዘዛቸውን ያስታወሱት ጄኔራሉ፣ በወቅቱ የተሠራው ስህተት ‹‹ዛሬ እንደ አገር ዋጋ እያስከፈለን ነው፡፡ በእኛ ጥፋት ምክንያት ሻዕቢያ ነፍስ ዘርቷል፤›› ሲሉም አክለዋል፡፡
ከጦርነቱ በኋላ በነበሩት 18 ዓመታት ‹‹የትግራይን ሕዝብን አጠፋለሁ፣ ኢትዮጵያን እወጋለሁ›› የሚል የጠላት ኃይል ከጀርባ እያለ ዝምታ መመረጡ ትልቅ ስህተት እንደነበር ተናግረዋል፡፡
አበበ ተክለ ሃይማኖት (ጆቤ)
በማከልም ‹‹ኢትዮጵያ የባህር በር ይገባታል፡፡ አሰብን መጠቀም ይገባታል፡፡ ነገር ግን በኃይል መሆን የለበትም፤›› ብለው፣ የቀጣናውን አሠላለፍ ለመቀየር ያለመ ጦርነት ቢሆን እንኳን፣ ‹‹ጨዋታው በኢትዮጵያና በኤርትራ አያበቃም፡፡ ጦርነት መጀመር ቀላል ቢሆንም ማቆም ከባድ ነው፤›› ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡ በሁለቱም ወገን የሚወሰድ የኃይል ዕርምጃ ቀጣናዊ አደጋው የጎላ እንደሆነም አክለዋል፡፡
የሕወሓት ምክትል ሊቀመንበር አቶ አማኑኤል አሰፋ በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል መቃቃር መፈጠሩን መታዘባቸውን ገልጸው፣ ቀይ ባህርን ማዕከል ያደረጉ የቃላት ልውውጦች መኖራቸውን ከሁለት ቀናት በፊት ተናግረዋል፡፡
‹‹ዝግጅት የሚመስሉ ወታደራዊ ትዕይንቶችን እያየን ነው፤›› ያሉት አቶ አማኑኤል፣ በጦርነት የሚፈታ ጥያቄ የለም ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያም ሆነ የኤርትራ መንግሥታት ነገሮችን በሰከነ መንገድ መመልከት እንዳለባቸው በማሳሰብ፣ ትግራይን የጦርነት ዓውድማ ማድረጉ ብቻ ሳይሆን የሚያመጣው ጂኦ ፖለቲካዊ አደጋም ከግምት መግባት እንዳለበት አሳስበዋል፡፡
ሒዩማን ራይትስ ኮንሰርን ፎር ኤርትራ የተባለው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት፣ የኤርትራ መንግሥት ከ60 ዓመት በታች ያሉ ዜጎች ለወታደራዊ ሥልጠና እንዲከቱ ለየአካባቢው አስተዳደሮች ትዕዛዝ ማስተላለፉን ከሳምንት በፊት ባወጣው መግለጫ ማስታወቁ ይታወሳል፡፡
-
Za-Ilmaknun
- Member
- Posts: 4486
- Joined: 15 Jun 2018, 17:40
Re: ኢትዮጵያና ኤርትራ ወደ ግጭት ሊያመሩ እንደሚችሉ የቀድሞ ከፍተኛ የጦር አዛዥ አበበ ተክለ ሃይማኖት (ጆቤ)ተናገሩ
The people are giving them the deaf ear so agew gala abiy and Esayas will have to scream louder about the war
the war they want is not getting the attention 
How will they start the war now? Will they force it onto the people. I think Esayas will send massive soldiers down to Tigray soon. There is no other way for them to create the war. What game plan is in their book is the big question
1. Are they trying to destroy the Eritrean identity after using it for 35 years to weaken Ethiopia? I think that is highly likely. They want to take over Eritrea and join Tigray with Eritrea and have the very minority agews take over the power hiding behind the majorities. If you notice lately, tplf leaders are openly saying they are waiting for the time to create a Tigray country. And south Africa is blocking them from becoming a country is what tplfs are saying now
2. They may let gala and agame fake army go through and march to Asmera and destroy the people that are pro Eritrea. And half agew control it in the name of agames
will agew Esayas cooperate, you bet!
I don't see why they would stop pushing for the war regardless of no attention from the people
How will they start the war now? Will they force it onto the people. I think Esayas will send massive soldiers down to Tigray soon. There is no other way for them to create the war. What game plan is in their book is the big question
1. Are they trying to destroy the Eritrean identity after using it for 35 years to weaken Ethiopia? I think that is highly likely. They want to take over Eritrea and join Tigray with Eritrea and have the very minority agews take over the power hiding behind the majorities. If you notice lately, tplf leaders are openly saying they are waiting for the time to create a Tigray country. And south Africa is blocking them from becoming a country is what tplfs are saying now
2. They may let gala and agame fake army go through and march to Asmera and destroy the people that are pro Eritrea. And half agew control it in the name of agames
I don't see why they would stop pushing for the war regardless of no attention from the people
Last edited by Union on 07 Mar 2025, 13:59, edited 4 times in total.
-
Za-Ilmaknun
- Member
- Posts: 4486
- Joined: 15 Jun 2018, 17:40
Re: ኢትዮጵያና ኤርትራ ወደ ግጭት ሊያመሩ እንደሚችሉ የቀድሞ ከፍተኛ የጦር አዛዥ አበበ ተክለ ሃይማኖት (ጆቤ)ተናገሩ
Those that beat the drums of war should be prepared to dance to it! OPDO seems to be pulling endless propaganda to move forward with the project of Greater Oromiya at the expenses of Ethiopians themselves. Ethiopia's primary enemy is now the OPDO rootless and ruthless monolithic regime. TPLF has been very successful in destroying the pillars of Ethiopia to finally absorbing the heavy losses of its reckless actions. Hopefully, the Abiy regime is now going straight in to its own death trap.
Re: ኢትዮጵያና ኤርትራ ወደ ግጭት ሊያመሩ እንደሚችሉ የቀድሞ ከፍተኛ የጦር አዛዥ አበበ ተክለ ሃይማኖት (ጆቤ)ተናገሩ
Now that the Somaliland agenda is paused for now, the new phase of agenda is the Agew agenda pushed by the ferenjis. Agew debretseon and agew getachew are ready to open the war on Eritrea. And Agew Esayas is ready to send his poor Eritrean soldiers down to Tigray to meet Tigreans and Ethiopian Habesha soldiers abducted by gala agew. The rest is a massacre!
Za-Ilmaknun wrote: ↑07 Mar 2025, 13:49Those that beat the drums of war should be prepared to dance to it! OPDO seems to be pulling endless propaganda to move forward with the project of Greater Oromiya at the expenses of Ethiopians themselves. Ethiopia's primary enemy is now the OPDO rootless and ruthless monolithic regime. TPLF has been very successful in destroying the pillars of Ethiopia to finally absorbing the heavy losses of its reckless actions. Hopefully, the Abiy regime is now going straight in to its own death trap.
-
Digital Weyane
- Member+
- Posts: 9834
- Joined: 19 Jun 2019, 21:45
Re: ኢትዮጵያና ኤርትራ ወደ ግጭት ሊያመሩ እንደሚችሉ የቀድሞ ከፍተኛ የጦር አዛዥ አበበ ተክለ ሃይማኖት (ጆቤ)ተናገሩ
ሰው ጥራ ቢሉት ጆቤን ጠራ። ጆቤ ኢትዮጵያውያን እርስ በእርስ እንዲባሉ ማድረግ አለብን ሲል ባደባባይ ተናግሯል።