Page 1 of 1

ኤርትራ የቀድሞ ሠራዊት አባላትን ለሥልጠና ስትጠራ ዜጎች ከአገር የሚወጡበትን መንገድ አጠበቀች (BBC)

Posted: 21 Feb 2025, 15:26
by Mesob
ኤርትራ የቀድሞ ሠራዊት አባላትን ለሥልጠና ስትጠራ ዜጎች ከአገር የሚወጡበትን መንገድ አጠበቀች

BBC, 21 የካቲት 2025

የኤርትራ መንግሥት የቀድሞ የሠራዊት አባላት ወደ የክፍሎቻቸው ለዳግም ሥልጠና እንዲመለሱ እና ሌሎችም ከአገር ለመውጣት የሚጠበቅባቸውን መስፈርቶች እንዳጠበቀ በኤርትራ ውስጥ እና በውጪ ሀገራት የሚገኙ የአገሪቱ ዜጎች ለቢቢሲ አረጋገጡ።

በዚህ መመሪያ መሠረት ከ60 ዓመት በታች የሚገኙ በኤርትራ ሠራዊት ውስጥ ያገለገሉ ዜጎች ተመዝግብው ወደ ማሠልጠኛ እንዲገቡ፤ እንዲሁም ከ50 ዓመት በታች የሆኑ ሰዎች ደግሞ ተገቢውን ፈቃድ ከሚመለከተው የመንግሥት አካል ሳያገኙ ከአገር እንዳይወጡ ያዛል።

ቢቢሲ ትግርኛ ያነጋገራቸው የአሥመራ ከተማ ነዋሪዎች ...


https://www.bbc.com/amharic/articles/c4g05y33k13o

=======================================