Page 1 of 1

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሜሪካ ትራንስፖርት ሚኒስቴር የገንዘብ ቅጣት ተላለፈበት

Posted: 19 Dec 2024, 19:27
by Za-Ilmaknun
የዩናይትድ ስቴትስ ትራንስፖርት ሚኒስቴር የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ኢቲሀድ ኤርዌይስ ሕግ በመጣሳቸው በገንዘብ እንዲቀጡ ወስኗል።

ሚኒስቴሩ ባለፈው ሐሙስ ባወጣው መግለጫ መሠረት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሜሪካው ዩናይትድ ኤርላይንስ መለያ (ኮድ) በመብረሩ 425 ሺህ ዶላር እንዲቀጣ ተወስኗል። :mrgreen:

የተባበሩት አረብ ኤምሬቶቹ ኤቲሀድ አየር መንገድ ደግሞ ጄትብሉ በተባለው የአሜሪካ አየር መንገድ መለያ ቁጥር በመብረሩ 400 ሺህ ዶላር ተቀጥቷል።

ሚኒስቴሩ በድረ-ገፁ ባወጣው መረጃ እንዳለው ሁለቱ አየር መንገዶች፤ በፌዴራል አቪዬሽን ባለሥልጣን (ኤፍኤኤ) የአሜሪካ አየር መንገዶች እንዳይበሩ በተከለከሉባቸው የአየር ክልሎች በመብረራቸው ነው ሕግ የጣሱት።

ሁለቱ አየር መንገዶች ከዚህ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸውም ተዘግቧል።

አቪዬሽን ኮንሲዩመር ፕሮቴክሽን የተባለው የዩናይትድ ስቴትስ ትራንስፖርት ሚኒስቴር ቢሮ ባደረገው ምርመራ ከአውሮፓውያኑ የካቲት 2020 እስካ ታኅሣሥ 2022 ባለው ጊዜ ነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ጥፋቱን ፈፅሟል የተባለው።

በዚህ ጊዜ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የዩናይትድ ኤርላይንስን ኮድ ተጠቅሞ ከኢትዮጵያ ጂቡቲ በርካታ በረራዎችን አድርጓል፤ ይህ የአየር ክልል ደግሞ የአሜሪካ አየር መንገዶች እንዳይበሩበት በፌደራል አቪዬሽን አስተዳደር ክልከላ የተደረገበት ነው ይላል።

የአፍሪካ ግዙፉ አየር መንገድ ይህንን ድርጊት የፈፀመው ከዩናይትድ ስቴትስ ትራንስፖርት ሚኒስቴር ፈቃድ ውጭ መሆኑን መግለጫው ያትታል።

ቅጣቱን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ቢቢሲ ምላሽ ለማግኘት ያደረገው ሙከራ አልተሳካም።


https://www.bbc.com/amharic/articles/cq8qzgn19ylo

Re: የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሜሪካ ትራንስፖርት ሚኒስቴር የገንዘብ ቅጣት ተላለፈበት

Posted: 19 Dec 2024, 23:42
by Union
:lol:

The US is now telling you it owns Ethiopia and eventually they are working to own everything in Ethiopia. Why do you think they are spending billions for the corridor limat :lol:

ባሪያ ሁላ አብይን ይደግፋል። ባንኩንም ገንዘቡንም ስራዎችንም፣ መከላከያ ተብዬውንም ከወረሱ ቦሀላ እያንዳድሽ አንገትሽ ይታነቃል :lol: :lol:

Re: የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሜሪካ ትራንስፖርት ሚኒስቴር የገንዘብ ቅጣት ተላለፈበት

Posted: 19 Dec 2024, 23:49
by Union
አብይን የሚደግፍ ባሪያ ነው የምንለው ለዛ ነው

Re: የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሜሪካ ትራንስፖርት ሚኒስቴር የገንዘብ ቅጣት ተላለፈበት

Posted: 20 Dec 2024, 14:25
by Za-Ilmaknun
Ethiopian Airlines downward spiral. Purchasing of scrap planes from China.


Re: የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሜሪካ ትራንስፖርት ሚኒስቴር የገንዘብ ቅጣት ተላለፈበት

Posted: 20 Dec 2024, 15:49
by Educator
Omg. Con artist satan Mamo Killo is ordering the airline to commit stupid crimes thinking he can get away with it just like all the mischief he got away with.

On the job training.
Za-Ilmaknun wrote:
19 Dec 2024, 19:27


በዚህ ጊዜ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የዩናይትድ ኤርላይንስን ኮድ ተጠቅሞ ከኢትዮጵያ ጂቡቲ በርካታ በረራዎችን አድርጓል፤ ይህ የአየር ክልል ደግሞ የአሜሪካ አየር መንገዶች እንዳይበሩበት በፌደራል አቪዬሽን አስተዳደር ክልከላ የተደረገበት ነው ይላል።

የአፍሪካ ግዙፉ አየር መንገድ ይህንን ድርጊት የፈፀመው ከዩናይትድ ስቴትስ ትራንስፖርት ሚኒስቴር ፈቃድ ውጭ መሆኑን መግለጫው ያትታል።

ቅጣቱን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ቢቢሲ ምላሽ ለማግኘት ያደረገው ሙከራ አልተሳካም።


https://www.bbc.com/amharic/articles/cq8qzgn19ylo