በተማፅኖ እና ምልጃ ወደ ክልል ስልጣን ለመመለስ የሚንከራተተው የትህነጉ ደብረፂ፣ በቀድሞ ተላላኪው ወግድልኝ በመባሉ፣ ለሌላ ተማፅኖ እየተዘጋጀ ነው!
Posted: 06 Dec 2024, 12:18
ሲያልቅ አያምር አሉ
ተራሮችን አንቀጠቀጥኩ እያለ በፈጠረው ቅዠት ራሱን አግዝፎ ለከፋ ውድቀት የተዳረገው የ ትህነግ ግባሶ፣ አሁን ደሞ ዘር ማጥፋት ፈፀሙብኝ ያላቸውን የ ኦህዴድ መኳንንቶች አባካችሁ፣ የ ክልሊቱን እንኳን ስልጣን ስጡኝ እያለ ለመለመን እግሩ እስኪቀጥን ወደ አዲስ አበባ እየተመላለሰ ነው፣፣ ጥጋብ ሲተነፍስ እንዲህ ነው 
በደብረጽዮን የሚመራው የህወሓት ቡድን በትግራይ እየተከሰተ ላለው ችግር የጊዜያዊ አስተዳደሩን ደካማነት በመግለጽ ለዚህም ፕሬዝዳንቱ ጌታቸው ረዳ ምክንያት መሆናቸውን በመግለጽ "ጌታቸው ተነስቶ ምክትሉ ጄኔራል ታደሰ ወረደ" ቦታውን እንዲይዙ ሃሳብ ማቅረባቸውን ጉዳዩን በቅርብት የተከታተሉት ተሳታፊ ተናግረዋል።
"ለጊዜያዊ አስተዳደሩ ሥራዎች እንቅፋት የሆናችሁት እናንተ [በደብረጽዮን የሚመራው የህወሓት ቡድን] ናችሁ" በማለት ምላሽ የሰጡት ጌታቸው ረዳ፣ በጦርነቱ የተፈናቀሉ ሰዎች ወደ ቀያቸው እንዳይመለሱ አድርገዋል ሲሉም ከሰዋቸዋል።
በድርጅቱ አባላት እና አመራሮች እንዲሁም በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እውቅናን ያላገኘው የህወሓት ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዶ አቶ ጌታቸው እና ሌሎችም ከፍተኛ አመራሮች ከፓርቲው ከተባረሩ በኋላ ደብረጽዮን የሚመሩት ቡድን የጊዜያዊ አስተዳደሩ መሪዎች ሥልጣን ላይ ጥያቄ ሲያነሳ ቆይቷል።
አቶ ጌታቸው የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንትነትን ቦታ የያዙት በህወሓት ውክልናቸው ነው በሚልም ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ የፌደራል መንግሥቱን ሲጠይቁ ነበር። አሁን ውዝግቡ እየተባባሰ ባለበት ጊዜም ችግሮችን ለመፍታት ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር በተደረገው ስብሰባ ደብረጽዮን ይህንኑ ጥያቄ አንስተዋል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/cy47n39n7lyo
በደብረጽዮን የሚመራው የህወሓት ቡድን በትግራይ እየተከሰተ ላለው ችግር የጊዜያዊ አስተዳደሩን ደካማነት በመግለጽ ለዚህም ፕሬዝዳንቱ ጌታቸው ረዳ ምክንያት መሆናቸውን በመግለጽ "ጌታቸው ተነስቶ ምክትሉ ጄኔራል ታደሰ ወረደ" ቦታውን እንዲይዙ ሃሳብ ማቅረባቸውን ጉዳዩን በቅርብት የተከታተሉት ተሳታፊ ተናግረዋል።
"ለጊዜያዊ አስተዳደሩ ሥራዎች እንቅፋት የሆናችሁት እናንተ [በደብረጽዮን የሚመራው የህወሓት ቡድን] ናችሁ" በማለት ምላሽ የሰጡት ጌታቸው ረዳ፣ በጦርነቱ የተፈናቀሉ ሰዎች ወደ ቀያቸው እንዳይመለሱ አድርገዋል ሲሉም ከሰዋቸዋል።
በድርጅቱ አባላት እና አመራሮች እንዲሁም በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እውቅናን ያላገኘው የህወሓት ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዶ አቶ ጌታቸው እና ሌሎችም ከፍተኛ አመራሮች ከፓርቲው ከተባረሩ በኋላ ደብረጽዮን የሚመሩት ቡድን የጊዜያዊ አስተዳደሩ መሪዎች ሥልጣን ላይ ጥያቄ ሲያነሳ ቆይቷል።
አቶ ጌታቸው የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንትነትን ቦታ የያዙት በህወሓት ውክልናቸው ነው በሚልም ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ የፌደራል መንግሥቱን ሲጠይቁ ነበር። አሁን ውዝግቡ እየተባባሰ ባለበት ጊዜም ችግሮችን ለመፍታት ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር በተደረገው ስብሰባ ደብረጽዮን ይህንኑ ጥያቄ አንስተዋል።
https://www.bbc.com/amharic/articles/cy47n39n7lyo