fasil1235 wrote: ↑22 Nov 2024, 06:21
say down down fano now
ከልጅነቴ ጀምሮ የማዉቀዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ፋኖዎች እንደ ኢትዮጵያ መላዕክት የተከበሩ ናቸዉ።
ይህም የፋሽስት ወረራ ግዜ በጀግንነት ቆመዉ ስለታገሉ ነዉ።
ወራሪዉ ተሸንፎ ከተመለሰ በኋላ ሰላማዊ ኑሮ ይኖሩ ነበረ። እንኳን ፋኖዎች ባንዳዎች ሃገር ዉስጥ ኣብረዉ፣ ፋኖዎች ከነበሩት ጋር በመጋባት ዝምድና ፈልገዉ በሰላም ይኖሩ ነበር።
ኣልፎ ኣልፎ ነዉ ትዝብት ነዉ ትርፉ እንደማለት ባንዳ ነበር የሚባለዉ።
እንደ ጥንት መላዕክቶች ኣልተዘከረላቸዉ እንጂ ምናልባትም ገድሎቻቸዉ እስከዚህ ዘመን ከሚዘከሩት በላይ ሊሆን ይችላሉ።
ጥይት ተፈጥሮ ያልነበረ ግዜ ነዉ ግዮርግስ በጦር ዘንዶ ገደለ ተብሎ ዘላለም የሚዘከረዉ።
እንደ እኔ አስተሳሰብ እህቱን የበላ ነብር ላይ ዘሎ ኣብረዉ ከነበሩት ጋር ነብሩን ገድሎ ጉማ ባሴን ሃዾ ካሱ ደዸቤ ያለዉ ገድሉ ከግዮርጊስ በላይ ነዉ።
የደምቢ ዶሎዉ ደጃዝማች ጆቴ ቱሉ ገድላቸዉ ምን ሆኖ እንደተሾሙ ባላዉቅም ፋኖ የነበሩ ሲመስለኝ ነዉ የኖርኩኝ።
ፋኖ የነበሩ ከሆነ ጋድላቸዉ ከግዮርጊስ የምያንስ ነበር?
ኣንድ ግዜ እንደ ጫወታ የጆቴ ወርቅ ነሃስ ኣይሁን ብዬ ነበር።
እነዚህ የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርዚቲ ተማሪዎች ደጃዝማች ጆቴ ቱሉ ፋኖ እንደነበሩ ኣያዉቁም ወይስ ስማቸዉን የማያከብሩ ተማሪዎች ናቸዉ?
ደጃዝማች እንጂ ራስ ኣልነበሩም የሚሉ ከሆነ በዚህ ዘመን ራስ ገዝ በሽበሽ ነዉ።
ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርዚቲ ስለ ቄለም የፌዴራል ራስ ገዝነትን እነዚህን ተማሪዎች ማስተማር ይችላል። እየተመራመሩ ራስ ገዙንም ሆነ ፌዴራሉን እንዴት ማሳደግ እንደሚቻል ማዘጋጀት ይችላል።
ኢትዮጵያ ዉስጥ ዩኒቨርዚቲዎችን ስለ ማስፋፋት ከብወንድሙ ጋር እዚሁ ወይም ሌላ መድረክ ላይ የተከራከርኩኝ ብዙ ዓመታት ኣልሆኑም።
እሱ ኣንገራጋሪ ነበር። ለማሳመን የተጠቀምኩትን ሀሳብ ሁሌም ኣልረሳም።
የሰዉ ኣዕምሮ እንደ ባዮሎጂካል መሺን ቢታሰብ ማሽኖቹን በብዛት ኣሰማራህ ማለት የበለጠ ዉጤት ማግኘት ነዉ የሚል ዐይነት ነበር።
የእነዚህን ተማሪዎች ኢትዮጵያ ዉስጥ እንደ መልዓክ የተከበረን ስም ዳዎን ዳዎን መፈክር ስሰማ ምን ከመድረሷ ምን መበጠሷ ኣስባለኝ።
ደጃዝማች ጆቴ ቱሉን ጨምሮ የኢትዮጵያ ፋኖዎች ለ ምርገ ነማ የቆሙ ኣልነበሩም?
እንደ እነ ሚስተር በትለር ደምቢ ዶሎ ድረስ ደርሰዉ እንደ እነ ዮሓንስ እና አብረሃም አባቶችን ስያዩዋቸዉ እነዛ የኢትዮጵያ አባቶች ለ ምርገ ነማ ከ ዋቀ ወይም ከ ቃሉ የተላኩ አያንቱዎች መስሏቸዉ ነበር?
በሃገሩ የቀረ ቃሉ ካለ ሚስተር በትለር ይዞ ደምቢ ዶሎ የገባ ወይም እዛ ዉስጥ ትቶ የወጣ ሰይጣን ካለ እነዚህ ተማሪዎች ሄደዉ ቢጠይቁት ይነግራቸዉ ይሆናል። ቃሉ ተገኝተዉ የተረሳ የሚስተር በትለርን ሰይጣን ካገኙ ይዉጣ እና ገተተ በትለር ይሁን ብለዉ ሕዝቡ ነፃ እንዲሆን ይሉ ይሆናል።
ሲነግራቸዉ ደጃዝማች ጆቴ ቱሉን ጨምሮ የኢትዮጵያ ፋኖዎችን ማክበር ይጀምሩ እና በተከበረ ፋኖ ስም መነገድ የለም ይሉ ይሆናል። ዳዎን ዳዎን ፋኖ ከማለት። ዳወን ዳወን ሴጠነ ሚስተር በትለር ማለት ካልቻሉ።
ከዚያም ምነዉ እንደተለከፈች ምን ወዲህ ጃንጆ፣ ወድያ ፋንዶ ማለት ብለዉ መጠየቅ ይችሉ ይሆናል።
የወለጋ አካል የሆነዉ ደምቢ ዶሎ ምንድነዉ ወለጋ የሌሎች ፋኖዎች ሃገር ሸዋ ዉስጥ በጥልቁ ሰርጎ ገብ ሆኗል ማለት ብለዉ መጠየቅ ይጀምሩ ይሆናል።
ወለጋ ሸዋ ዉስጥ በጥልቁ ሰርጎ ገብ ሆኗል ያለዉ ድፌንድዘትሩዝ ነዉ። ድሮ ሳይሆን ዘንድሮ። እዚሁ ፎረም ላይ።