መፈንቅለ መንግሥት በ ትግራይ ክልል! ጌታቸው የፀጥታ ኃይሉ ደብረ ጽዮን ላይ ዕርምጃ እንዲወስድ ጠየቀ
Posted: 18 Nov 2024, 19:11
የደብረ ጽዮንቡድን ወደ ለየለት ሥርዓት አልበኝነት ተሸጋግሯል በማለት የገለጸው የፕሬዚዳንቱ ጽሕፈት ቤቱ፣ ‹‹በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች በሚገኙ መንግሥታዊ መዋቅሮች ላይ ሕገወጥ ምደባዎችን በማካሄድና ጫና በመፍጠር የጊዜያዊ አስተዳደሩን ሥራዎች በማደናቀፍ ላይ ተጠምዷል፤›› ብሏል፡፡
ሁኔታው ተባብሶ በመቀጠሉ ምክንያት፣ ጊዜያዊ አስተዳደሩ መሰል ሥርዓቱ አልበኝነት ከአቅሙ በላይ በመሆኑ የትግራይ ፀጥታ ኃይል፣ የፍትሕ አካላትና ባንኮች እየታየ ያለውን ሕገ መንግሥቱን የጣሰ አካሄድ ተገንዝበው ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስቧል፡፡
በደብረ ጽዮን (ዶ/ር) የሚመራው ሕወሓት ከሁለት ወራት በጊዜያዊ አስተዳደሩ የሚደረገውን ሹም ሽር በተደጋጋሚ ሲቃወም ቆይቷል፡፡ በታችኛው መዋቅር የሚገኙ ምክር ቤቶች ስብሰባ በማካሄድ አዳዲስ ምደባዎችን እንደማይቀበልና አቶ ጌታቸው ረዳን ጨምሮ በካቢኔያቸው ውስጥ ያሉት አምስት ሰዎች በድርጅቱ መባረራቸውን በተደጋጋሚ ቢገልጽም፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ጽሕፈት ቤት ግን ‹‹በግላጭ መፈንቅለ መንግሥት እየተካሄደብኝ ነው፤›› በማለት በተደጋጋሚ በሚያወጣቸው መግለጫዎች እየገለጸ ነው፡፡
https://www.ethiopianreporter.com/135505/
ሁኔታው ተባብሶ በመቀጠሉ ምክንያት፣ ጊዜያዊ አስተዳደሩ መሰል ሥርዓቱ አልበኝነት ከአቅሙ በላይ በመሆኑ የትግራይ ፀጥታ ኃይል፣ የፍትሕ አካላትና ባንኮች እየታየ ያለውን ሕገ መንግሥቱን የጣሰ አካሄድ ተገንዝበው ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስቧል፡፡
በደብረ ጽዮን (ዶ/ር) የሚመራው ሕወሓት ከሁለት ወራት በጊዜያዊ አስተዳደሩ የሚደረገውን ሹም ሽር በተደጋጋሚ ሲቃወም ቆይቷል፡፡ በታችኛው መዋቅር የሚገኙ ምክር ቤቶች ስብሰባ በማካሄድ አዳዲስ ምደባዎችን እንደማይቀበልና አቶ ጌታቸው ረዳን ጨምሮ በካቢኔያቸው ውስጥ ያሉት አምስት ሰዎች በድርጅቱ መባረራቸውን በተደጋጋሚ ቢገልጽም፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ጽሕፈት ቤት ግን ‹‹በግላጭ መፈንቅለ መንግሥት እየተካሄደብኝ ነው፤›› በማለት በተደጋጋሚ በሚያወጣቸው መግለጫዎች እየገለጸ ነው፡፡
https://www.ethiopianreporter.com/135505/