The Humiliation of Agames Continues: ህወሓት በልዩ ሁኔታ መመዝገብ እንጂ የቀድሞው ህልውናው እንደማይመለስለት ምርጫ ቦርድ አስታወቀ
Posted: 10 Aug 2024, 03:14
It was only a couple of years back when Agames were adamant that TPLF=Tigray and vice versa. And now, they are finding it out that TPLF has lost its legitimacy both with the federal government and its own people. This is yet another historical blow. TPLF has to register as a new party. All its properties have probably been confiscated.



ህወሓት በልዩ ሁኔታ መመዝገብ እንጂ የቀድሞው ህልውናው እንደማይመለስለት ምርጫ ቦርድ አስታወቀ
9 ነሐሴ 2024
ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) የቀድሞው ሕጋዊ ሰውነቱ እንዲመለስ ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት እንዳላገኘ እና በልዩ ሁኔታ እንዲመዘገብ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መወሰኑን ገለጸ።
ምርጫ ቦርዱ ለፓርቲው የሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት በልዩ ሁኔታ መስጠቱን ዛሬ አርብ ነሐሴ 3/ 2016 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
ፓርቲው ሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫው የተሰጠው በኃይል እንቅስቃሴ ውስጥ ሲሳተፉ ለነበሩ የፖለቲካ ቡድኖች ሕጋዊ ዕውቅና መስጠትን አስመልክቶ በዚህ ዓመት ግንቦት መጨረሻ በጸደቀው የፓርቲዎች ምዝገባ እና ሥነ ምግባር ማሻሻያ አዋጅ መሠረት መሆኑንም ቦርዱ አመልክቷል።
ህወሓት በፖለቲካዊ ውሳኔ የነበረው ሕጋዊ ሰውነት እንዲመለስለት እንጂ እንደ አዲስ መመዝገብ እንደማይፈልግ የፓርቲው ቃል አቀባይ አቶ አማኑኤል አሰፋ ከዚህ ቀደም ለቢቢሲ መናገራቸው ይታወሳል።
ህወሓት የቀድሞው ሕጋዊ ሰውነቱ እንዲመለስ ሐምሌ 19/2016 ዓ.ም. ለቦርዱ አመልክቶ የነበረ ቢሆንም፣ በጸደቀው ማሻሻያ መሠረት የቀድሞ ሕጋዊ ሰውነትን መመለስ የሚል ባለመኖሩ ጥያቄው ተቀባይነት አለማግኘቱ ተገልጿል።
የተሻሻለው አዋጅ “በአመፅ ተግባር ተሠማርቶ ለተሠረዘ ፓርቲ የቀድሞውን ኅልውና መልሶ የሚሰጥ የሕግ ድንጋጌ ያልያዘ በመሆኑ ቦርዱ በድጋሚ የቀረበለትን ሕጋዊ ሰውነት ወደነበረበት እንዲመለስ የሚለውን ጥያቄ አልተቀበለውም” ብሏል።
አቶ አማኑኤል “ሕጋዊ ሰውነት እንዴት እንደሚመለስ በምርጫ ሕጉ ግልጽ ስላልሆነ ተጨማሪ [የሕግ] ማዕቀፍ በማዘጋጀት የተሰረዘው ሕጋዊ ሰውነት እንዲመለስ ይደረጋል የሚል ንግግር ነበር” ሲሉ ለቢቢሲ ከዚህ ቀደም ተናግረው ነበር።
ይህ የአዋጅ ማሻሻያ፤ “የተሰረዘውን ሕጋዊ ሰውነት ለመመለስ የሚያስችል ሳይሆን እንደ አዲስ ለመመዝገብ የሚያስችል” መሆኑን አቶ አማኑኤል ጠቅሰው በጉዳዩ ላይ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ንግግር መጀመሩን ጠቁመው ነበር።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያጸደቀው ይህ አዋጅ፤ ኃይልን መሠረት ባደረገ የአመጽ ተግባር ተሳትፎ የነበረ የፖለቲካ ቡድን በልዩ ሁኔታ በፓርቲነት የሚመዘገብበትን ሂደት በዝርዝር ያስቀመጠ ነው።
የአዋጅ ማሻሻያው፤ የፖለቲካ ቡድኑ “ሕገ መንግሥታዊ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን አክብሮ ለመንቀሳቀስ መስማማቱ በሚመለከተው የመንግሥት አካል ከተረጋገጠ፣ የፖለቲካ ቡድኑ በልዩ ሁኔታ እንደ ፖለቲካ ፓርቲ ሊመዘገብ ይችላል” ሲል ይደነግጋል።