Page 1 of 1

የ ኦሮሚያ መንግሥት ወሰድኩት ባለው እርምጃ ከ OLF እገታ የተለቀቁት ተማሪዎች መካከል ባለፉት ቀናት 16ቱ ገንዘብ ከፍለው መለቀቃቸው ተሰማ :)

Posted: 07 Aug 2024, 17:32
by Za-Ilmaknun
ምንም እንኳ መንግሥት ወሰድኩት ባለው እርምጃ ተማሪዎቹን ማስለቀቁን ቢናገርም፤ በመጀመሪያዎቹ ሳምንታት ቢቢሲ ያናገራቸው ቤተሰቦች እና ምንጮች ግን ተማሪዎቹ እንዳልተለቀቁ እና የማስለቀቂያ ገንዘብ እየተጠየቀባቸው እንደሆነ ተናግረዋል።

ሰኔ ወር መጨረሻ ላይ በሕዝብ ማመላለሻ አውቶብሶች ወደ አዲስ አበባ ሲጓዙ በኦሮሚያ ክልል ገርበ ጉራቻ አካባቢ የታገቱት የደባርቅ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች አንድ በእገታ ስር አንድ ወር አልፏቸዋል።

ከ100 በላይ ተማሪዎች ሰኔ 26/2016 ዓ.ም. ከአማራ ክልል ተነስተው ወደ ዋና ከተማዋ በመጓዝ ላይ እያሉ በጎሃ ጽዮን እና ቱሉ ሚልኪ መካከል በታጣቂዎች መታገታቸው ይታወሳል።

ባለፈው ሳምንትም በእገታ ስር ከሚገኙ ተማሪዎች መካከልም 16 የሚሆኑ በመቶ ሺዎች የሚቆጠር የማስለቀቂያ ገንዘብ ከፍለው መለቀቃቸውን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ባለፈው ረቡዕ ሐምሌ 24/2016 ዓ.ም. ከ100 ሺህ እስከ 500 ሺህ ብር የከፈሉ 11 ተማሪዎች መለቀቃቸውን ለደኅንነታቸው ሲሉ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈቀዱ ሁለት የተለቀቁ ተማሪዎች ቤተሰቦች ለቢቢሲ አረጋግጠዋል።
Such is the kind of Government we have back home. Some in this forum are naïve enough to take at face what the the Abiy :mrgreen: government says. We painfully remember the Amhara kids en-route from Wellega university who were abducted by the savage Shene/OPDO and never heard from since. However, the same government told us at the time that the kids were rescued.

https://www.bbc.com/amharic/articles/cd9ddvz2q8yo