ሰኔ ወር መጨረሻ ላይ በሕዝብ ማመላለሻ አውቶብሶች ወደ አዲስ አበባ ሲጓዙ በኦሮሚያ ክልል ገርበ ጉራቻ አካባቢ የታገቱት የደባርቅ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች አንድ በእገታ ስር አንድ ወር አልፏቸዋል።
ከ100 በላይ ተማሪዎች ሰኔ 26/2016 ዓ.ም. ከአማራ ክልል ተነስተው ወደ ዋና ከተማዋ በመጓዝ ላይ እያሉ በጎሃ ጽዮን እና ቱሉ ሚልኪ መካከል በታጣቂዎች መታገታቸው ይታወሳል።
ባለፈው ሳምንትም በእገታ ስር ከሚገኙ ተማሪዎች መካከልም 16 የሚሆኑ በመቶ ሺዎች የሚቆጠር የማስለቀቂያ ገንዘብ ከፍለው መለቀቃቸውን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ባለፈው ረቡዕ ሐምሌ 24/2016 ዓ.ም. ከ100 ሺህ እስከ 500 ሺህ ብር የከፈሉ 11 ተማሪዎች መለቀቃቸውን ለደኅንነታቸው ሲሉ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈቀዱ ሁለት የተለቀቁ ተማሪዎች ቤተሰቦች ለቢቢሲ አረጋግጠዋል።
Such is the kind of Government we have back home. Some in this forum are naïve enough to take at face what the the Abiy
https://www.bbc.com/amharic/articles/cd9ddvz2q8yo