Page 1 of 1

ትሕነግ ሊያካሂድ ያቀደው ጠቅላላ ጉባኤ ከአባላቱ ተቃውሞ ገጠመው :)TPLF በ50 ዓመት ታሪኩ አጋጥሞት የማያውቀው ፈተና

Posted: 07 Aug 2024, 16:59
by Za-Ilmaknun
በደቡብ ትግራይ ዞን ከሚገኙት 14 ወረዳዎች 12ቱ የፓርቲው ጉባኤ በዚህ ጊዜ እንዳይካሄድ ወስነዋል። :mrgreen:
በደቡብ ምሥራቅ ዞን እንደርታ ወረዳ የፓርቲው አባላት “ጉባኤው በዚህ ጊዜ እንዳይካሄድ” የሚል ውሳኔ ያሳለፈ ሲሆን፣ በስብሰባው የ24 ቀበሌዎች ተወካዮች መገኘታቸውን ምንጮች ለቢቢሲ ገልጸዋል
የእንደርታ ወረዳ አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ስላስ ሃፍቱ ሕዝቡ የተወሳሰበ ችግር ውስጥ ባለበት እና በፓርቲው ውስጥ አንድነት በሌለበት ሁኔታ ጉባኤ መካሄድ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ እንዳልሆን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
የፓርቲው ሊቀመንበር እና ምክትላቸው አንድ ባልሆኑበት፣ የቁጥጥር ኮሚሽኑ ሊቀመንበሩን ጨምሮ አባላቱ በሌሉበት ጉባኤ ማካሄድ ተገቢ አይደለም” ብለዋል።

ወይዘሮ ስላስ ተሰብሳቢዎቹ ፓርቲው በአባላቱ የቀረበውን ሀሳብ እንዲያዳምጥ መማጸናቸውንም አስታውሰዋል።

“ከዚህ በፊት የአባላቱን ድምጽ የሚሰማ ድርጅት ነበር፤ ፓርቲው ወደ ቀድሞው ባህሪው ሊመለስ ይገባል። ከዚህ ውጪ ዴሞክራሲያዊ አካሄድ አይደለም።”

በክልሉ ውስጥ “ከፌዴራል መንግሥት እና ከምርጫ ቦርድ እውቅና ሳይሰጠው የህወሓት ጉባኤ መካሄድ ለሕዝብ አጥፊ እና የማይጠቅም ነው” የሚል አቋም የያዙ ሰዎች እንደነበሩ ተናግረዋል።

“የቁጥጥር ኮሚሽኑ አባላት በሌሉበት፣ ሁለት ሰዎች ከአዘጋጅ ኮሚቴው በቀሩበት፣ በአጠቃላይ በፌዴራል መንግሥት ላይ እምነት በሌለበት ሁኔታ እና ብዙ ሰዎች ከአዘጋጅ ኮሚቴው ራሳቸውን ባገለሉበት ሁኔታ ውስጥ ጉባኤ ማካሄድ አደጋ ሊያመጣ እንደሚችል መረጃዎች አሉ፤ እኔም ይህንን ተገንዝቤ ነው ራሴን ያገለልኩት” ይላሉ።

https://www.bbc.com/amharic/articles/cpdll7v6jvpo

Re: ትሕነግ ሊያካሂድ ያቀደው ጠቅላላ ጉባኤ ከአባላቱ ተቃውሞ ገጠመው :)TPLF በ50 ዓመት ታሪኩ አጋጥሞት የማያውቀው ፈተና

Posted: 07 Aug 2024, 17:03
by Za-Ilmaknun
የማይጨው ከተማ ከንቲባ የማነ ንጉሤ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ከሁሉ በፊት ፓርቲው ጉባኤውን አካሂዶ የሕዝቡን መልካም አስተዳደር ጥያቄ ቢመልስ የሚል እምነት እንደነበራቸው፣ ነገር ግን ህወሓት ያደረጋቸውን ረዥም ጊዜ የወሰዱ ስብሰባዎችን ከተመለከቱ በኋላ “ድርጅቱ አመራር በኔትወርክ እና በአካባቢያዊነት እየታመሰ እንደሆነ” መገንዘባ መቻላቸው ይናገራሉ።

“አንድ ቡድን ሌላውን ማሸነፍ የሚፈልግበት ሁኔታ አለ፤ በሁለተኛ ደረጃ ይህ ኔትወርክ ለረጅም ጊዜ የቆየእና ስር የሰደደ ነው” ሲሉም የቁጥጥር ኮሚሽኑ ሦስት አባላት ከወጡ ጉባኤውን የሚመራው ማን ነው? የሚል ጥያቄ አንስተዋል።
:mrgreen: ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መግለጫ ህወሓት በሕጉ መሠረት ካልተመዘገበ ወደ ሌላ ሁኔታ እንሸጋገራለን ብሏል። ስለዚህ መግባባት ላይ አልተደረሰም ማለት ነው የሚል ትርጉም ሰጥቶናል” ብለዋል።

Re: ትሕነግ ሊያካሂድ ያቀደው ጠቅላላ ጉባኤ ከአባላቱ ተቃውሞ ገጠመው :)TPLF በ50 ዓመት ታሪኩ አጋጥሞት የማያውቀው ፈተና

Posted: 09 Aug 2024, 19:49
by Za-Ilmaknun