አዳነች አቤቤ የዘመኑ ንግስት ጣይቱ፤
Posted: 01 Aug 2024, 13:26
Axumezana wrote: ↑06 Nov 2020, 13:40Our TPLF forces preemptively disabled the Northern Command and confiscated all military hardware. I wonder where they're heading next.
viewtopic.php?f=2&t=235755

Meleket wrote: ↑30 Jul 2024, 03:19እርግጥ ነው
ምንም እንኳን ከንጹሓን ኤርትራዉያን በተዘረፈ ሃብት ኣማካኝነት ቢሆንም እንኳ፡ የህዳሴውን ግድብ የመሰረት ድንጋይ በማስቀመጥ ነፍስኄር ኣቶ መለስ ዜናዊን
የአዲስ ኣበባን ከተማ ገጽታ በመቀየር ደግሞ ዶ/ር ኣርከበ ዕቁባይንና የአሩሲዋን ንግሥት ወ/ሮ አዳነች አበቤን ኣመራር ኣለማድነቅ ኣይቻልም።
“ይህ በእንዲህ እንዳለ” . . . .
የአዲስ አበባ ህዝብ የንጹህ ውሃ ኣቅርቦት ችግር እዬተቀረፈ ነውን?
የሸገር ህዝብ የኤሌክትሪክ ሃይል ቅርቦት ችግር እየተፈታ ነውን?
የፍንፍኔ ህዝብ የደረቅና ፍሳሽ ቆሻሻ ችግር እየተሻሻለ ነውን?
የበራራ ህዝብ ከቤቱ ኣለአግባብና በግድ እዬተፈናቀለ ነውን? በሚገባስ እዬተካሰ ነውን? ብሎ መጠዬቅ የወግ ነው።
ብዙ ያፍሪካ ሃገራት መዲኖች እነ የአሩሲዋ ንግሥት እነ ወ/ሮ ኣዳነች ኣበቤ እያስመዘገቡት ያለውን የሚጨበጥ የሚታይና የሚዳሰስ ድል እንደሚናፍቁ ዜጎቻቸው አፍ አውጥተው ቢናገሩ ኃጥያት ኣይደለም።
ዶ/ር ኣብዪ ኣሕመድም በታሪካዊዋ ጎርጎራ ላይ ያደረጉትን ስራ ኣይተን እጅግ አድንቀናል።
የጣና ሃይቅ የእንቦጭ ጉዳይስ የት ደርሶ ይሆን? እስቲ ውስጥ ኣዋቂዎች ሹክ በሉን!
እኛ ኤርትራውያን የመሀልና የመስመር ዳኞች መቼም ስለ ኤርትራችን ብቻ ሳይሆን ስለ ጎረቤቶቻችን በሙሉ መልካም መልካሙን መመኘት ኣምላክ የቸረን መለያችንና ባህርያችን ነው።፡ ከሁሉም ጎረቤቶቻችን መልካም ተግባር ትምህርት መቅሰም፡ ከስህተቶቻቸው መማር ወዘተ ደግሞ መብታችን መሆኑን ስናሳውቅ በኤርትራዊ ጭዋነት ኩራትና ትህትና ጭምር ነው።
እስቲ ለጨዋታ ያህል
የአሩሲዋ ንግሥት ወ/ሮ ኣዳነች ኣበቤ አዲስ አበባን ለማስዋብ ደፋ ቀና በማለታቸው ብቻ ከእቴጌ ጣይቱ ጋር ለማመሳሰል የተሞከረ ይመስላል
ለመሆኑ ወ/ሮ ኣዳነች አበቤ እንደ እቴጌ ጣይቱ ኣንደኛና ሁለተኛ ባለቤት ተብሎ የሚገለጽ የትዳር ታሪክ ኣላቸውን?
ለመሆኑሳ ወ/ሮ ኣዳነች አበቤ ከባለቤታቸው በዕድሜ ይበልጣሉን?
እርግጥ ነው እቴጌ ጣይቱ ከአጤው ጤንነት መጓደል በኋላ፡ ፈላጭ ቆራጭ ለመሆን ዳድቷቸው ነው መሰል ጐንደሬ ዘመዶቻቸውን ወደ አዲስ አበባ እያስጠሩ በዙሪያቸው ለማደራጀት ጥረት በማድረጋቸው ከሸዋ መኳንንትና መሳፍንት ጥርስ ውስጥ በመግባት በወጥመድ ለመያዝ ተገደዋል። የአሩሲዋ ንግሥትም የአዲስ አበባ ከንቲባ የሆኑበት ሂደት ያልተስማማቸው አካላት ተቃውሞ አድርገውባቸው እንደነበር እናውቃለን።
በነገራችን ላይ ዋናው ቁምነገር እኝህ የአሩሲዋ ንግሥት ጦቢያን ከውስጥ ወራሪ ለማዳን ምን ሚና ኣበርክተዋል? ጣይቱ መቼም ወራሪውን ጣልያንን በመመከት ረገድ ሁነኛ ስራ እንደሰሩ ነው ታሪክ የሚያወሳው።
የአሩሲዋ ንግሥትስ አዲስ አበባን ከውስጥ ወራሪ ታድገዋታል ወይስ ራሳቸው የአሩሲዋ ንግሥት ከህግ ውጭ በሆነ ሁኔታ የአሩሲ ዘመዶቻቸውን ኣስፍረውባታል? መልሱን ኣዋቂዎች ንገሩን!
ለማንኛውም ክብር መልካም ሰላማዊ ስራንና ልማትን ሰርተው ለሚያሳዩ የህዝብ ኣመራሮች በሙሉ!
የጎንደሯ የሙዚቃ ፈርጥ ኣስቴር ኣወቀ "ስምክን ሳላነሳው . . ." የምትለውን ዜማ እንዴት ነበር ያንጐራጐረቸው! ወዳጃችን Axumezana ደግሞ ለየት ባለ ቅኝት “ለአሩሲዋ ንግሥት” ይህን እያንጐረጐረላት ይመስላል። መቼም ስሟን ሳያነሳው ኣይውልም። ቢያንስ ቢያንስ በየሳልስቱ።