Page 1 of 1

" ' የቤት ኪራይ ጨምሩ ' ወይም ' ቤቱን ልቀቁ ' የሚል ግፊት ከደረሰባችሁ ደውላችሁ ጠቁሙኝ " - የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ

Posted: 26 Jun 2024, 10:15
by Educator
" ' የቤት ኪራይ ጨምሩ ' ወይም ' ቤቱን ልቀቁ ' የሚል ግፊት ከደረሰባችሁ ደውላችሁ ጠቁሙኝ " - የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ

በአዲስ አበባ ፤  ' ከአከራይ ተከራይ  የውል ስምምነት ' ጋር በተያያዘ ተከራዮች የሚገጥማቸውን ማንኛውም ችግር ጥቆማ ሊሰጡ እንደሚችሉ የከተማው የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አሳውቋል።

ቢሮው ማንኛውም አከራይ ከመጋቢት 24 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ የቤት ኪራይ መጨመርም ሆነ ተከራይን ማስወጣት ፈፅሞ የተከለከለ መሆኑን አስገንዝቧል።

ከዚህም ጋር በተያያዘ ተከራዮች የቤት ኪራይ ጭማሪ አልያም ' ቤቱን ይልቀቁልኝ ' የሚል ግፊት ከአከራዮች ከደረሰባቸው በስልክ ቁጥር +251118722917 / +251118553820 ላይ በመደወልና ጥቆማቸውን በመስጠት መብታቸውን ማስከበር እንደሚችሉ ገልጿል።

በሌላ በኩል ፤ ሰኔ 1 ላይ የጀመረው የአከራይ ተከራይ የውል ስምምነት ሊጠናቀቅ  14 ቀናት የቀሩት ሲሆን ዜጎች በአቅራቢያቸው በሚገኙት ወረዳዎች በማቅናት ምዝገባ እንዲያካሂዱ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

አከራዮች የውል ስምምነቱን ሳይፈጽሙ እስከ ሶስት ወር ድረስ ከቆዩ የሁለት ወር የቤት ኪራይ እንዲከፍሉ እንደሚደረግ ተገልጿል።

መንግስት ጥናት በማድረግ በሚቀጥለው ዓመት ሰኔ ወር ላይ የዋጋ ጭማሪ እንደሚያደርግ አሳውቋል።

አከራይ የቤት ኪራይ ዋጋ ጭማሪ ማድረግ የሚችለው በዓመት አንዴ መንግስት በሚያወጣው ተመን ብቻ እንደሚሆን ተነግሯል።

#TikvahEthiopia
#HousingDevelopmentandAdministration

@tikvahethiopia

Re: " ' የቤት ኪራይ ጨምሩ ' ወይም ' ቤቱን ልቀቁ ' የሚል ግፊት ከደረሰባችሁ ደውላችሁ ጠቁሙኝ " - የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ

Posted: 26 Jun 2024, 13:23
by Dama
This seeminly renter protection regulation is an edict, not a law passed by parliament.
Abiy Ahmed and his mistress Abebe are just notriously greedy to swindle the poor pensioners who rent out a room or two out of their residence, in order to cop with inflated prices of foods and other basic necessities of life.