ከልማት ባንክ ብድር በወሰዱ የትግራይ ባለሀብቶች ንብረት ላይ ሐራጅ መውጣት ጀመረ
Posted: 06 Jun 2024, 11:50
ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ ብድር የወሰዱ የትግራይ ክልል አንዳንድ ባለሀብቶች፣ በንብረታቸው ላይ ሐራጅ እየወጣባቸው መሆኑንና ሥጋት ውስጥ መውደቃቸውን፣ የትግራይ ክልል ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
በትግራይ ክልል በጦርነቱ ንብረታቸው የወደመባቸው ባለሀብቶች እስካሁን መንግሥት ያለባቸውን ዕዳ እንዲሰርዝ ወይም አስፈላጊውን የሥራ ማስኬጃ ብድር እንዲመቻችላቸው ውሳኔ ባለማስተላለፉ፣ ባለሀብቶቹ የመኖሪያ ቤቶቻቸው በሐራጅ እንዳይሸጡ ሥጋት ውስጥ መውደቃቸውን የትግራይ ክልል ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዳንኤል መኮንን ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡
በጦርነቱ ወቅት ንብረቶቻቸው የወደሙባቸውን ሁለት ባለሀብቶችን ንብረት ለመሸጥ ልማት ባንክ በቅርቡ ሐራጅ ማውጣቱንና ሁኔታው በዚሁ ከቀጠለ ቤቶቻቸውን አስይዘው የተበደሩና በጦርነቱ ወቅት ሙሉ ለሙሉ ንብረታቸው የወደመባቸውም ባለሀብቶች የዚህ ዕጣ ፈንታ ተካፋይ እንደሚሆኑ አክለው ገልጸዋል፡፡
https://www.ethiopianreporter.com/130157/
በትግራይ ክልል በጦርነቱ ንብረታቸው የወደመባቸው ባለሀብቶች እስካሁን መንግሥት ያለባቸውን ዕዳ እንዲሰርዝ ወይም አስፈላጊውን የሥራ ማስኬጃ ብድር እንዲመቻችላቸው ውሳኔ ባለማስተላለፉ፣ ባለሀብቶቹ የመኖሪያ ቤቶቻቸው በሐራጅ እንዳይሸጡ ሥጋት ውስጥ መውደቃቸውን የትግራይ ክልል ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዳንኤል መኮንን ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡
በጦርነቱ ወቅት ንብረቶቻቸው የወደሙባቸውን ሁለት ባለሀብቶችን ንብረት ለመሸጥ ልማት ባንክ በቅርቡ ሐራጅ ማውጣቱንና ሁኔታው በዚሁ ከቀጠለ ቤቶቻቸውን አስይዘው የተበደሩና በጦርነቱ ወቅት ሙሉ ለሙሉ ንብረታቸው የወደመባቸውም ባለሀብቶች የዚህ ዕጣ ፈንታ ተካፋይ እንደሚሆኑ አክለው ገልጸዋል፡፡
https://www.ethiopianreporter.com/130157/