ያኔ የኦህዴድ-ብልፅግና አካሄድ ለዘብ ያለና ፋኖን ፊት ለፊት ከመቀጥቀጥ፣ ጃዊሳ በሚል የጥቂቶች የሽፍትነት አካሄድ አድርጎ የማሳየት ነበር. የአገዛዙ ቀመር ወዲህ ነው. ፋኖ ካልን ከህዝብ ያጣላናል ነው.
አሁን ግን፣ ጃዊሳ ማለቱን ትቶ፣ ፋኖ እያለ በቀንደኛ ካድሬዎቹ፣ ፕሮፓጋንዳውን እየሰራበት ነው
ብዙ ሰው ይህን የፕሮፓጋንዳ ሽፍት ያስተዋለ አልመሰለኝም? ለነገሩ ብዙ ግዜ ብዙ ሰው አያስተውልም. አገዛዙም የቆየው ለዚህ ነው.
እኔ ግን ይህ የፕሮፓጋንዳ ሽፍት ትልቅ እንደምታ አለው ባይ ነኝ.
አሁን ፋኖን ፋኖ ብሎ ፕሮፓጋንዳ፣ በስትራቴጂ ደረጃ እየሰራበት ይገኛል. ግን ፋኖ ደግሞ፣ በድፍን አማራ፣ ከዛም ባሻገር፣ የሚደገፍ የህዝብ አካል ነው.
ምን ይታይሃል/ሻል?
p.s. ቀንደኛ ካድሬዎቹ: ሲሳይ አጌና፣ ስዩም ተሾመ እንዲሁም ዘሃበሻ፣ ፈታ፣ ሃቅና ሳቅ እና መሃል ሜዳ.