Page 1 of 1

BBC:-ኬሪያ ኢብራሂምን እና ሙሉ ገብረእግዚአብሔር ከህወሓት ፓርቲ ተባረሩ

Posted: 23 Feb 2024, 14:21
by Za-Ilmaknun
የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ በጦርነቱ ወቅት ለፌደራል መንግሥቱ እጅ ሰጥተው ምሥጢር አሳልፈው ሰጥተዋል ያላቸውን ሁለት የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላቱን ከፓርቲው ማባረሩን አስታወቀ።

ህወሓት ከድርጅቱ ያባረራቸው ሁለቱ ሴት የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት፣ ከጦርነቱ በፊት በፌደራል መንግሥቱ ውስጥ ከፍተኛ ሥልጣን ላይ የነበሩት ኬሪያ ኢብራሂም እና ሙሉ ገብረእግዚአብሔር ናቸው። የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ ሐሙስ የካቲት 14/2016 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ ኬሪያ ኢብራሂም እና ሙሉ ገብረእግዚአብሔር “ለጠላት እጃቸውን ሰጥተው ምሥጢር አሳልፈው ሰጥተዋል” ተብለው በድርጅቱ ደንብ መሠረት ከማዕከላዊ ኮሚቴ እና ከህወሓት አባልነት እንዲባረሩ ወስኗል።

What is next? :|

https://www.bbc.com/amharic/articles/crg76jeznd3o