ህወሓት ከድርጅቱ ያባረራቸው ሁለቱ ሴት የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት፣ ከጦርነቱ በፊት በፌደራል መንግሥቱ ውስጥ ከፍተኛ ሥልጣን ላይ የነበሩት ኬሪያ ኢብራሂም እና ሙሉ ገብረእግዚአብሔር ናቸው። የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ ሐሙስ የካቲት 14/2016 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ ኬሪያ ኢብራሂም እና ሙሉ ገብረእግዚአብሔር “ለጠላት እጃቸውን ሰጥተው ምሥጢር አሳልፈው ሰጥተዋል” ተብለው በድርጅቱ ደንብ መሠረት ከማዕከላዊ ኮሚቴ እና ከህወሓት አባልነት እንዲባረሩ ወስኗል።
What is next?
https://www.bbc.com/amharic/articles/crg76jeznd3o