Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Naga Tuma
Member+
Posts: 6026
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

ኦሮሞ ማነዉ?

Post by Naga Tuma » 09 Feb 2024, 18:29

ይህ ቀላል ጥያቄ ኣዕምሮኣቸዉ ላሳይንሳዊ አስተሳሰብ ለበራላቸዉ ብቻ ነዉ። በግዜ ያልተገደበ እዉነትን ከስህተት ኣበጥረዉ ማወቅ ለሚችሉ ማለት ነዉ።

ወደ ጥያቄዉ ሳልገባ በፊት ሶስት መሠረታዊ ግንዛቤዎቼን ላስቀምጥ።

ኣንደኛ በሶስት ቀላል መስፈርቶች አፋን ኦሮሞ በመባል የሚታወቀዉ ቋንቋ በአለም ላይ ከሚታወቁት ብዙ ቋንቋዎች ወይ ይበልጣል ወይ እኩል ነዉ።

ሁለተኛ ኢትዮጵያ ተብላ ለረጅም ግዜ የታወቀች ሃገር የብዙ የሰዉ ጎሳዎች ሽብርቅ ነች ብዬ ኣስባለሁ።

ሶስተኛ ከረጅም ታሪክ በላይ አደዋ ሙሉ በሙሉ ባይሆንም ይህን ሽብርቅ ኣንድ ወገን ወይም ወገነ ኣድርጓል ብዬ ኣስባለሁ።

ከሆነ ይህን ቀላል ጥያቄ ምን ይመልሳል?

ለበርካታ ዓመታት ይህቺን ታሪካዊ የሰዉ ጎሳዎች ሽብርቅ ተሻሽላ ትደግ እና ተናግታ ለኦሮሞ የምትሆን ኣዲስ ሃገር ትወለድ በሚል ክርክር ተሽመድምዳ እንደነበር ኣስታዉያለሁ። ብዙዎች ነበሩ ይህን መሽመድመድ ያስተዋሉት።

ኢትዮጵያ እያለሁ ነበር የመጫ እና ቱለማ መሪ የነበሩት ኮሎኔል አለሙ ቅጤሳ ቅርንጫፍ እንጂ ግንድ ኣይገነጠልም ብሎ ቪኦኤ ላይ ሲናገሩ የሰማሁኝ።

መጫ እና ቱለማ እስከዛሬ ስሙን ያልቀየረ የተወሰኑ የኢትዮጵያ ጎሳዎች ኣንጋፋ ድርጅት ነዉ ማለት የሚቻል ይመስለኛል።

በእኔ ግምት ኢትዮጵያን ኣሽመድምዷት ከነበረዉ ክርክር ተሻሽላ ትደግ የሚለዉ አስተሳሰብ ኣፈትልኮ ሲወጣ ነዉ ከመሽመድመድ የወጣችዉ። ለዚህ ደግሞ ዕዉቀት ከድንቁርና ተበጥሮ ነዉ።

ዛሬ ከርቀት ሳነብ የሰዉ ጎሳዎች ሽብርቋ ኢትዮጵያ ዉስጥ ኦሮሞ ስልጣን በዛበት እንጂ ኣነሰበት የሚል ያለ ኣይመስለኝም።

ቢሆንም ሽብርቋ ዉስጥ የጎሳዎቿ ማንነት ዉዥንብር ዉስጥ ተሽመድምዳ ያለች መሆኑን ነዉ የማነበዉ።

ሽብርቋ ከዚህም መሽመድመድ ወጥታ በርታ ማደግን የምትቀጥለዉ ማንነቷን በዕዉቀት ኣበጥራ ዕዉቀት ኣፈትልኮ ሲወጣ ነዉ ብዬ ኣስባለሁ።

ለዚህ ነዉ ኦሮሞ ማን ነዉ ብዬ የዕዉቀት ጥያቄን የምጠይቀዉ።

ልጅ ሆኜ መደበኛ ትምህርት ያልተማሩ ኣባቶች እና እናቶች የአከባቢዎቸቸዉን ጎሳዎች ኣበጥረዉ እንደምያዉቁ ኣዉቃለሁ። ገበሮዎች እና ቦረናዎች በሚባሉ ጎሳዎች የሚታወቁ ናቸዉ።

እ ኣ አ በ1991 ትግርኛ ተናጋሪ የኢትዮጵያ ጎሳዎች ታጥቀዉ አከባቢዉ ሲደርሱ ሌላ ጎሳ አከባቢዉን ወረረ ብሎ ነዉ ብዙዎች ኣብረዉ የተነሱት።

ከዛ መነሳሳት በኋላ ነበር ኣጭር የትግል መንገድ ላይ ካየሁዋቸዉ ሰዎች ዉስጥ የተወሰኑትን ብዙ ግዜ የማስታዉሰዉ። በግለሰብ ደረጃ እኔን ከመነሳሳት ያረጋጋኝ እና ሰላማዊ ትግል ያስጀመረኝ የቻርተሩ መፈረም ነበር።

መንገድ ላይ ተገናኝተን የቻርተሩ መፈረም መንገዳችንን ከለያየዉ ዉስጥ ነጋሳ ኩምሳ የሚባል ሰዉን ኣስታዉሳለሁ። ከዛ በኋላ የት እንዳለ ኣላዉቅም።

ትግል ብሎ ሲጥር ሶስት ወራት ሳይሞሉ ሰዎች ሁለቴ ታዝበዉት እንደነበረ ኣስታዉሳለሁ።

የመጀመርያዉ ሰዎችን ሰብስቦ ስያስተምር በርካታዎች ማንነቱን እና ባህሪዉን ታዝበዉ እንደነበር ኣስታዉሳለሁ። በተለይ ኣብሮን የነበረ የምስራቅ ወለጋ ሰዉ ፌዝን ኣልረሳም።

ከዛን ቀን በኋላ ተመልሶ ስያስተምር ማየቴን ኣላስታዉስም።

ሁለተኛዉ ሰዎች በጣም የታዘቡት የማይገባዉ ስጦታ ተሰጠዉ ብለዉ ነዉ። የሰጪዉንም ማመዛዘን ችሎታ ጭምር ነበር የታዘቡት።

እኔ አላማ ብሎ ለሚታገል ክብር ኣለኝ። ስህተትን ኣስተዉሎ ካረመ ይመሰገናል።

ይህን ታሪክ እዚህ የማነሳዉ ለኣንድ ጥያቄ ብቻ ነዉ።

ነጋሳ ኩምሳ ኦሮሞ ነዉ? ነጋሳ ኩምሳ ኦሮሞ ካልሆነ ኦሮሞ ማን ነዉ?

ከቦረና እና አኙዋ የተወለደ ኢትዮጵያዊ ከሆነ የሰዉ ጎሳዎች ሽብርቋ ኢትዮጵያ አካል የማያደርገዉ ምን ምክንያት ኣለ?

ፕሮፌሰር መረራ ጉድናን ኢትዮጵያ እያለሁ ነዉ ጽሑፉን ያነበብኩኝ። ተገቢ ያልሆኑ ቃላቱ ከብደዉኝ ስለኢትዮጵያ ፖለትካ ትንተናዉን ኣከበርኩኝ።

ኢትዮጵያ እያለሁ በዛ ጽሑፉ ምክንያት መወገድ ኣለበት የሚል መንገድ ላይ ኣጋጥሞኝ በጣም ነቅፌዉ ፊቱን ኣዙሮ ከአጠገቤ ሄደ። ሰዉየዉ የፖለትካ ዶክተሩ ጎሳ ነኝ ባይ ነበር።

እዚህ አሜሪካ ዉስጥ ብያንስ አምስት ግዜ የፖለትካ አመለካከቱን እና ማንነቱን የነቀፉ ኣጋጥመዉኝ ነቅፌኣቸዋለሁ።

የሰፈሩ ሰዉ ፕሮፌሰሩ በማንነቱ ኦሮሞን እወክላለሁ ማለቱ ተገቢ ኣይዴለም ብሎ በንቀት ሲናገር ሰምቻለሁ፣ ኣይቻለሁ።

የአከባቢዉ ሰዎች ማንነቱን ጥያቄ ዉስጥ ስያስገቡ ሰምቼ ነቅፌኣለሁ።

ኦቦ ቡልቻ ደመክሳ የፖለትካ ምሁሩ ከኣቋቋሙት ጋር ተመሳሳይ የሆነ አዲስ የፖለትካ ድርጅት ስያቋቋም እንተርኔት ዉስጥ የተዋወቁኝ የከበርኳቸዉ የአከባቢዉ ሰዉ ስልክ ደዉለዉልኝ ሲጋብዙኝ የነበረዉ ዉስጥ ገብታችሁ ለምን ኣታጠናክሩትም ብዬ ጠየኳቸዉ።

የፖለትካ ምሁሩን ሳይሆን ማንነቱን ሲዘልፉ ታዝቤ በትህትና ስልካቸዉን ኣቆምኩኝ።

የፖለትካ ሳይንስ ተምሮ ለኦሮሞ እታገላለሁ ብሎ ዓመታትን ያሳለፈ ኢትዮጵያዊ የሰፈሩ እና የአከባቢዉ ሰዎች ማንነቱን የሚጠይቁ ከሆነ ኦሮሞ ማነዉ?

ከዓመታት በፊት ሰዉ ቤት ተጋብዤ ሰዎች ስለታሪክ ስያወሩ ሰማሁ። በልጅነት ከሰማሁኝ ታሪክ ጋር ያልተጣጣመ መሆኑን ስገነዘብ እያመነታሁ በጣም ቀላል ጥያቄ ጠየኩኝ። ያመነታሁኝ ልታዘቡኝ የሚችሉ እናትም ተጋብዘዉ አጠገባችን የነበሩ ስለሆነ ክርክር ተጀምሮ ይከራከራል እንዳይሉኝ ነበር።

ጥያቄዬ በታሪክ አምስት መቶ ዓመታትን ወደ ኋላ ተመልሶ ስለማወቅ ነበር።

ጥያቄዬ ከሰሙት ዉስጥ ኣንዱ ወድያዉ ፊቱን ከእኔ ኣዞረ። የተማረ ነዉ። እስከመጨረሻ። ጥያቄዬ እንዳልገባዉ ኣስተዉዬ ኣሳዘነኝ።

ሌላዉ ጥያቄዬ ገብቶት ይወያዩ ወደነበሩት ዞሮ ልብ በሉ አይነት ነገር ሲናገር ሰማሁ። መደበኛ ትምህርት መከታተሉን ኣላዉቅም።

ከዛ በኋላ ዉይይቱ መቀጠሉን ኣላስታዉስም።

ጥያቄዬን ሰምቶ ከእኔ ፊቱን ያዞረዉ ከእኔ ርቆ ከዓመታት በኋላ በድንገት ባዕድ ሃገር ኣረፈ የሚል መርዶ ሰምቼ ደነገጥኩኝ። ኣዘንኩኝ። በደመነፍስ ከእኔ ባይርቅ ይተርፍ ነበር ኣልኩኝ።

እስከዛሬ በምን ምክንያት በድንገት እንደኣረፈ ኣላዉቅም። ልብ በሉ ብሎ የነበረዉን ሰዉ ከዛ መርዶ በኋላ ላነጋግረዉ ሞክሬ እስከዛሬ ድረስ ኣልተሳካልኝም።

ከእኔ ከራቀበት ግዜ ጀምሮ በድንገት እስከ ኣረፈበት ቀን ምን ዉስጥ እንዳለፈ ኣላዉቅም።

ከዓመታት በፊት የጠየኩኝን ጥያቄ የሚከተለዉ ቪድዮ መልሶታል።



ይህ የሃገር ሰዉ፣ ከቤተሰቡ ለብቻዉ ተምሮ የወጣ፣ ሁለት ታዳጊ ልጆቹን ባዕድ ሃገር ትቶ ኣረፈ።

መቃብሩ ላይ የኣረፈዉ ጎሳ ወገን ነኝ የሚል ወንድ ልጁ ፊት ጥቁር አፈር ሲወረዉር ኣይቼ በዉስጤ ባህል ዬለሽ ጭንጋፍ ኣልኩት።

በኦሮሞ ስም እታገላለሁ ብሎ በባዕድ ሃገር የወገኑ ጎሳ ነኝ በሚል ጭንጋፍ ወንድ ልጁ ፊት መቃብሩ ላይ ጥቁር አፈር የሚወረዉር ከሆነ ኦሮሞ ማን ነዉ?

ያለፈበትን የፖለትካ መንገድ ባላዉቅም በድንገት ክብሩን ጠብቆ የሄደዉ ከቦረና ተነስቶ ወልሶ የደረሰዉ ሊበን አከባቢ ተወልዶ ያደገ ቢሆንም በየት በኩል ከቦረናዉ ሰዉ ሊበን ጋር እንደሚገናኝ እስከዛሬ ኣላዉቅም።

ከኣሁን በፊት እዚሁ ፎረም ላይ ቦረና ነዉ የኦሮሞ አባት ወይስ ኦሮሞ ነዉ የቦረና አባት ብዬ ጠይቄ ነበር። ኣንድ ያገኘሁኝ መልስ ቦረና ነዉ የኦሮሞ አባት የሚል ነበር።

ታድያ ቦረና የኦሮሞ አባት ከሆነ በልጅ ስም ከመታወቅ ለምን በአባት ስም ኣይታወቅም፧

ኦሮሞ ነኝ ብሎ የሚዘፍነዉ ታደለ ሮባ ከቦረናዉ ሰዉ ሊበን ጎሳ የተወለደ ነዉ?

ቦረና የኦሮሞ አባት ከሆነ፣ ታደለ ሮባ በከፊልም ሆነ በሙሉ ከቦረና ያልተወለደ ከሆን ኦሮሞ ነኝ ብሎ መዝፈን ምን ትርጉም ኣለዉ?

ይህ ሁሉ ጥያቄ መሠረታዊ መልስ ተገኝቶ ኢትዮጵያ በማነንት ጥያቄ ተሽመድምዳ ካለችበት እንድትወጣ ነዉ።

ኢትዮጵያ ዉስጥ የማንነት ጥያቄ ትግል በክርስትና ትምህርት ምክንያት የዛሬ ሁለት ሺህ ዓመታት ጀምሮ እያዘገመ መምጣቱን ኢትዮጵያን በሰፊዉ ያጠናዉፕሮፌሰር ዶናልድ ኤን ለቪን ኣስቀምጠዋል።

ከኢትዮጵያ እስከ ግብጽ፣ ሴኔጋል፣ እና ግሪክ በሰፊዉ ኣጥንቷል የተባለዉ ኢትዮጵያዊዉ ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን የኢትዮጵያ ሕዝብ በኣብዛኛዉ ኣንድ መሠረት እንዳላቸዉ ለታሪክ ኣስቀምጧል።

ካልዘነጋሁ ፕሮፌሰር ኤፍሬም ኢሳቅም ተመሳሳይ ግንዛቤ እንዳላቸዉ ሰምቻለሁ።

ለዚህ ብዙ ኣመላካቸች ኣሉ። ኣንድ ጎሳ ቆንቆ ሲል ሌላ ጎሳ ቋንቋ ሲል ከጥንት ጀምሮ ባይተዋወቁ ነዉ? ኣንድ ጎሳ አፍ ሲል ሌላ ጎሳ አፋን የሚለዉ ከጥንት ጀምሮ ባይተዋወቁ ነዉ? ከጥንት ጀምሮ የሚተዋወቁ ጎሳዎች ቢሆኑ ኣይዴለም ኼረ እግዝኣብኼር ዉስጥ የተገኘዉ?

ከጥንት ጀምሮ ቢተዋወቁ ከሆነ የሰዉ ጎሳዎች ሽብርቋ ኢትዮጵያ መብራቷ ቀርቶ በጎሳዎች የማንነት ትግል ለምን ትሽመደመዳለች?
Last edited by Naga Tuma on 09 Feb 2024, 18:48, edited 1 time in total.

Union
Senior Member
Posts: 11460
Joined: 14 Feb 2021, 15:24

Re: ኦሮሞ ማነዉ?

Post by Union » 09 Feb 2024, 18:39

Anbeta qorchame

Nice try.

Tesfaye gebre ebab :lol:

Mind your shi't'hole first :lol:

Your Eritrean women are prostitutes all over Africa including in Addis, you are here talking about gala :lol: :lol:

Naga Tuma
Member+
Posts: 6026
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

Re: ኦሮሞ ማነዉ?

Post by Naga Tuma » 25 Feb 2024, 04:33

ኢትዮጵያ ምን ያህል ጥንታዊ እንደሆነች ለማወቅ የሚከተሉትን አምስት ቃላት ማወቅ ኣይበቃም፧?

ጎፍታ ጎይታ ጌታ ጎድ
አባ ኣብ አባት አቡ
ሰበ ሰብ ሻብያ
ዌረረ ወረራ ዋር
ሴረ ሴራ ሸርያ

እነዚህ ቃላት ለስንቶቹ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች የጋራ ናቸዉ?

እነዚህን ቃላት በጋራ የሚጠቀሙ ጎሳዎች ቃላቱ የእኔ የሰዉ ጎሳ እንጂ የኣንተ የሰዉ ጎሳ ኣይዴለም መባባል ይችለሉ?

ስንቶቹ የኢትዮጵያ የሰዉ ጎሳዎች ናቸዉ ለእነዚህ አምስት ቃላት ሌሎች ቃላት ያላቸዉ?

የማያዉቁትን ማንበብ ለማወቅ ነዉ።

የዚህ የሰዉ ጎሳ፣ የዛ የሰዉ ጎሳ ከሚለዉ ኣዙሪት ያላቅቃል። ኣያላቅቅም?

ከኣዙሪቱ መላቀቀ ወደበለጠ እድገት ይወስዳል። ኣይወስድም?

እድገት ሲመጣ መዘለፍ ይጠፋል። ኣዙሪቱ ዉስጥ ገብተን እሩቅ ኣህጉር በሚኖሩ ሰዎች ክፉ ዘለፋ ኣንዴም መዘለፍ በጣም ብዙ ነዉ።

Naga Tuma
Member+
Posts: 6026
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

Re: ኦሮሞ ማነዉ?

Post by Naga Tuma » 13 Aug 2024, 17:48

ቅርብ ግዜ ከሜላህ ምን ማለት ነዉ ብዬ ብጠይቅ አከም ኣለህ ማለት ነዉ የሚል መልስ ሰማሁ።

ወድያዉ አከም፣ ሐኪም፣ አከመ የሚሉትን ቃላት ኣስታወስኩ።

ጥያቄዉ የበለጠ ጥልቅ ይሆናል፣ ለሳይንሳዊ አስተሳሰብ ኣእምሮዎቻቸዉ ለበራላቸዉ።

Naga Tuma
Member+
Posts: 6026
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

Re: ኦሮሞ ማነዉ?

Post by Naga Tuma » 13 Aug 2024, 18:55

Dama:

Did you remove your response? I remember reading one.

I have a suggestion for you if you care to consider.

I have noticed your shallow knowledge. If you keep being infuriated while your shallow knowledge crumbles under your feet, you wouldn’t be helping yourself because knowledge will keep advancing.

Dama
Member
Posts: 4291
Joined: 22 Jun 2024, 21:05

Re: ኦሮሞ ማነዉ?

Post by Dama » 13 Aug 2024, 19:07

Naga Tuma wrote:
13 Aug 2024, 18:55
Dama:

Did you remove your response? I remember reading one.

I have a suggestion for you if you care to consider.

I have noticed your shallow knowledge. If you keep being infuriated while your shallow knowledge crumbles under your feet, you wouldn’t be helping yourself because knowledge will keep advancing.
Yea, I called you ebbat Galla, and then removed it wanting to be politically correct.

I mean, how can you ask "What's Oromo?' For your level, is this not an elementary question? Especially for someone from Ethiopia that has been discussing about nations and how they are formed at least since 1974.
kebt sew!

Naga Tuma
Member+
Posts: 6026
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

Re: ኦሮሞ ማነዉ?

Post by Naga Tuma » 13 Aug 2024, 19:51

Dama wrote:
13 Aug 2024, 19:07
Naga Tuma wrote:
13 Aug 2024, 18:55
Dama:

Did you remove your response? I remember reading one.

I have a suggestion for you if you care to consider.

I have noticed your shallow knowledge. If you keep being infuriated while your shallow knowledge crumbles under your feet, you wouldn’t be helping yourself because knowledge will keep advancing.
Yea, I called you ebbat Galla, and then removed it wanting to be politically correct.

I mean, how can you ask "What's Oromo?' For your level, is this not an elementary question? Especially for someone from Ethiopia that has been discussing about nations and how they are formed at least since 1974.
kebt sew!
How did someone who was born to Borana and Agnua parents become an Oromo? By the 1974 revolution?

Dama
Member
Posts: 4291
Joined: 22 Jun 2024, 21:05

Re: ኦሮሞ ማነዉ?

Post by Dama » 13 Aug 2024, 19:54

Naga Tuma wrote:
13 Aug 2024, 19:51
Dama wrote:
13 Aug 2024, 19:07
Naga Tuma wrote:
13 Aug 2024, 18:55
Dama:

Did you remove your response? I remember reading one.

I have a suggestion for you if you care to consider.

I have noticed your shallow knowledge. If you keep being infuriated while your shallow knowledge crumbles under your feet, you wouldn’t be helping yourself because knowledge will keep advancing.
Yea, I called you ebbat Galla, and then removed it wanting to be politically correct.

I mean, how can you ask "What's Oromo?' For your level, is this not an elementary question? Especially for someone from Ethiopia that has been discussing about nations and how they are formed at least since 1974.
kebt sew!
How did someone who was born to Borana and Agnua parents become an Oromo? By the 1974 revolution?
Not an evolution. It's an adoption. A choice.

Naga Tuma
Member+
Posts: 6026
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

Re: ኦሮሞ ማነዉ?

Post by Naga Tuma » 13 Aug 2024, 21:39

Dama wrote:
13 Aug 2024, 19:54
Naga Tuma wrote:
13 Aug 2024, 19:51
Dama wrote:
13 Aug 2024, 19:07
Naga Tuma wrote:
13 Aug 2024, 18:55
Dama:

Did you remove your response? I remember reading one.

I have a suggestion for you if you care to consider.

I have noticed your shallow knowledge. If you keep being infuriated while your shallow knowledge crumbles under your feet, you wouldn’t be helping yourself because knowledge will keep advancing.
Yea, I called you ebbat Galla, and then removed it wanting to be politically correct.

I mean, how can you ask "What's Oromo?' For your level, is this not an elementary question? Especially for someone from Ethiopia that has been discussing about nations and how they are formed at least since 1974.
kebt sew!
How did someone who was born to Borana and Agnua parents become an Oromo? By the 1974 revolution?
Not an evolution. It's an adoption. A choice.
A choice. Got it. You are entitled to your choice. However, you are not entitled to impose your choice on others. It is that simple.

Naga Tuma
Member+
Posts: 6026
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

Re: ኦሮሞ ማነዉ?

Post by Naga Tuma » 13 Aug 2024, 21:48

ከዓመታት በፊት ቦረን ሰገል፣ ገበሮ ሰገልተመ የሚል አባባል ኣነበብኩኝ። ቦረና ዘጠኝ ነዉ፣ ገበሮ ዘጠና ነዉ ማለት ነዉ።

ከዚህ አባባል ተነስተን ገበሮዎች ኦሮሞዎች ናቸዉ ማለት ይቻላል?

ከኦነግ በፊት ተቋቁሞ ዕዉቅናን ያገኘዉ መጫ እና ቱለማ መረዳጃ ማህበር ስሙን ኣልቀየረም። ለምንድነዉ ወደ ኦሮሞ ያልቀየረዉ? ኣለመቀየሩ ስህተት ነዉ ለማለት ኣይዴለም። ላለመቀየሩ ምክንያት ኣለዉ ወይ ለማለት ነዉ።

Naga Tuma
Member+
Posts: 6026
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

Re: ኦሮሞ ማነዉ?

Post by Naga Tuma » 14 Aug 2024, 14:48

Sadacha Macca writes:

We've been calling ourselves ilma Orma loooong before the German j krapf came to Ethiopia dude. You are showing how ignorant you are when you post such nonsensical things dude. It's okay to NOT know. But it's not okay to pretend that you know something.

According to him, Ilma Orma is the root of the word Oromo. I do not know if this is verifiable.

እልመ ወንድ ልጅ ማለት ነዉ።
ኦርመ ባዕድ ማለት ነዉ።

ሰደቸ መጫ ያለዉ እዉነት ከሆነ ማን ነዉ እልመ ኦርመ ያለዉ? ቦረና ነዉ? ቦረና ከሆነ እልመ ኦርማን እንደ ሌላ ሰዉ ጎሳ ነዉ የምያዉቀዉ ማለት ነዉ። ኣይዴለም? ቦረና ሌላ ጎሳን እልመ ኦርማ ካለ ያ ጎሳስ እራሱን የምያዉቅበት ስም ወይም ስሞች የሉም?

የሚገርመዉ ሌሎች ኢትዮጵያንን ኦርመ ወይም ባዕድ ያለዉ ኢትዮጵያዊ ኦርመ ወይም ባዕድ እባላለሁ ማለት ነዉ።

ለዚህ ነዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ስንት የሰዉ ጎሳዎች እንዳሉ ኣጥንቶ ማወቅ የምያስፈልገዉ።

Naga Tuma
Member+
Posts: 6026
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

Re: ኦሮሞ ማነዉ?

Post by Naga Tuma » 09 Sep 2024, 15:05

ሳይንቲስቶች የሆናችሁ ለዚህ ቀላል ጥያቄ መልስ ኣግኝታችሁ ሕዝቡን ማስተማር ትችላላችሁ?

ለምሳሌ የሚሆን በጣም ቀላል ማስተዋልን በቅርቡ እዚህ ፎረም ላይ ጽፌ ነበር።

የኦሮምኛ ቃል ኩት፣ የአማርኛ ቃል ቁረጥ ( ኩረት) እና የእንግልዘኛ ቃል ከት (ኩት) ተመሳሳይ ትርጉም ኣላቸዉ።

መሠረታቸዉ ኣንድ ቃል ከሆነ ኦሮሞ ማን ነዉ?

ኦሮምኛ ተናጋሪዉ ኩት ባይ ነዉ?
ወይስ አማርኛ ተናጋሪዉ ቁረጥ (ኩረት) ባይ ነዉ?
ወይስ እንግሊዘኛ ተናጋሪዉ ከት (ኩት) ባይ ነዉ?

Naga Tuma
Member+
Posts: 6026
Joined: 24 Apr 2007, 00:27

Re: ኦሮሞ ማነዉ?

Post by Naga Tuma » 19 Mar 2025, 17:12

ይህን ርዕስ ጀምሬ ከሰነበተ በኋላ ነዉ ቢዛሞ የሚባል ቃልን ለመጀመርያ ግዜ የሰማሁኝ። እስከ ቅርብ ግዜ ድረስ ቃሉን መስማቴን ኣላስታዉስም።

ስለ ቢዛሞ ታሪክ እዚህ ፎረም ላይ የተጻፈዉ ይህን ርዕስ ኣስታወሰኝ። ጉዲ ሰዲ ኣስብሎኝ ሌላ ጥያቄ ኣስጠየቀኝ።

የኦሮሞ ጥናት ማህበር ኣራማጆች የነበሩት ፕሮፌሰር ኣስፋዉ በየነ፣ ፕሮፌሰር መኩርያ ቡልቻ፣ እና ፕሮፌሰር አሰፋ ጃለታ የጎሳቸዉ መሠረት ቢዛሞ ነዉ ወይስ ቦረና ነዉ? ወይስ ከሁለቱም ጎሳዎች ናቸዉ?

ቢዛሞዎች ከሆኑ እንዴት ኦርመ እንደተባሉ ኣያዉቁም?

ብዙ ምርምሮችን ስያደርጉ ስለ ቢዛሞ ተመራምረዉ ያሳተሙት ጥናት ኣለ?

የዚህ ርዕስ አላማ የጥንታዊ ኢትዮጵያን ታሪክ በሳይንሳዊ አስተሳሰብ ጥልቀቱን እንድናዉቅ ነዉ።

ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ጥልቀቱን ኣዉቀዉ በየቋንቋዉ ኢትዮጵያ ሃገራችን፣ ኢትዮጵያ ብየ ኬኘ ማለት ሲችሉ ተባብረን እናሳድጋት ማለት ይከተላል።

ethiopianunity
Member+
Posts: 9960
Joined: 30 Apr 2007, 17:38

Re: ኦሮሞ ማነዉ?

Post by ethiopianunity » 20 Mar 2025, 11:53

Naga,

This Oromo entity for sure not the Oromo we are used to that practices non Ethiopian symbol. By the way to bring Democracy in Ethiopia (of course was never perfect ), you don’t have to destroy your original identity which was Ethiopian flag, Geez writing, Geda, Sufi Muslim and Orthodox. The Oromo radicals today are not

Post Reply