እላ ፊ እላሜ
Posted: 05 Jan 2024, 19:12
አፋን ኦሮሞ ዉስጥ ጥልቅ የሆኑ አስተሳሰቦችን ከምያንጸባርቁት ዉስጥ እላ ፊ እላሜ ኣንዱ ነዉ ብዬ ኣስባለሁ።
እላ ማለት እይ ወይም ተመልከት ማለት ነዉ፣ በኣድናቆት ጭምር።
እላሜ ማለት እስቲ ስማ ወይም እስቲ እይ እንደማለት ነዉ። ከግሰጻ ጋር። ይታረም እንደማለት ነዉ።
ከዚህ የበለጠ ወይም የጠለቀ ማብራርያ ይኖረዉ ይሆናል። እኔ የገባኝን ያህል ነዉ የሞከርኩኝ። የምሞክረዉ።
በእንግልዘኛ እላ Look! ማለት ይሆናል። እላሜ Look here እንደማለት ይሆናል።
ለዚህ ጥልቅ አስተሳሰብ ግልጽ ምሳሌ ይሆናል ብዬ የማስብ የሽግግር ግዜ ኦቦ ሌንጮ ለታ ሲናገር በዜና የሰማሁኝ ነዉ።
ቃል በቃል ባይሆንም ኣንድ ቀን የሰማሁትን ንግግሩን በደንብ ኣስታዉሳለሁ።
መማር እንፈልጋለን። ከዚህ የተማርነዉ ምንም የለም ነበር ያለዉ።
የተናገረዉ ከማስታዉሰዉ ከተለየ ስህተቱ የእኔ ማስታወስ ይሆናል።
መማር እንፈልጋለን ማለቱ በኣድናቆት እላ ያምያስብል ነዉ። ያስባለኝ ነዉ። መማር እንፈልጋለን የሚል ባለስልጣን የተለመደ ኣልነበረም። ኣላስታዉስም ነበር። እናስተምራችሁ ባይ ባለስልጣን ነበር የስልጣን ባህሉ።
መማር እንፈልጋለን ማለቱን ሰምተህ እላ ብለህ ኣጣጥመህ ሳታበቃ በፍጥነት ከዚህ የተማርነዉ ምንም የለም ማለቱን ስትሳማ በቅጽበት አረ እባክህ የምያስብል ነበር። ያስባለኝ ነዉ።
በእላ ፊ እላሜ መማር እንፈልጋለን ያልከዉ እላ ያስብላል። ከዚህ የተማርነዉ ምንም የለም ያልከዉ እላሜ ያስብላል። ለምሳሌ ከዚህ ምንም የተማርነዉ ዬለም ከማለት ከእኛም እንድትማሩ እንመክራለን ብትል ኖሮ ይሻል ነበር ማለት ነዉ።
ሀሳብ የሰዉን ኣዕምሮን በቀላሉ ይረታል። በቀላሉም ግትር ያደርገዋል።
ሁሉም ሰዉ በተለያየ ደረጃ ኢጎ የምትባል ነገር ኣለዉ። በኣማርኛ ወይም አፋን ኦሮሞ ትርጉሙን ኣላዉቅም። ምናልባት ከማን ኣንሼ ይገልጸዉ ይሆናል።
እላ ስለ ግል ሳይሆን ስለ ሌላ ነዉ። ከማን ኣንሼ ስለ ሌላ ሳይሆን ስለ ግል ነዉ። ይህቺን ልዩነት ብቻ ማስተዋል መግባባትን የምያበዛ ይመስለኛል።
ጥልቅ ባህል ያለዉ ሕዝባችን እላ ፊ እላሜ ይላል። ስለ ግል ሳይሆን ስለ ሌላ ያወሳል። እኛ ትምህርት ቤት ደርሰን ከማን ኣንሼ እንላለን። ስለ ሌላ ሳይሆን ስለ ግል እናወሳለን። ሁሌ ባይሆንም ብዙ ግዜ። ለክርክር የሚበቃ ግዜ። ለክርክር የበቃ ለክርክር መቀጠል ይበቃል።
በተለይ ብዙ ሳይለፉበት ኣዲስ ሀሳብ ሲሰሙ ሳይገባቸዉ ግትር የሚሆኑ ይበዛሉ። በጥበብ እንዲገባቸዉ ማድረግ ይቻላል።
የኣጋጠመኝ ምሳሌ ኣለ። በለዉጥ ግዜ የነበረ ዕድር እንድመራ ተመርጬ የመተዳደርያ ደንብ ኣዘጋጀሁለት። አባላቱ ሀሳብ በመስጠት ማሻሻል ይችሉ ነበር። ጥቂቶች ሀሳብ በመጨመር እንዲሻሻል ኣድርገዋል።
ለማጽደቅ ተሰበሰብን። ኣንድ አባል ኣንድ አንቀጽ ጉድለት ኣለዉ የሚል ሀሳብ ኣቀረበ።
ወድያዉ ኣንብቦ እና የራሱን ሀሳቦች ጨምሮበት የነበረ አባል ጉድለት የለዉም ኣለ። ስብሰባዉን እየመራሁ ጉድለት ኣለዉ እና ዬለዉም የሚል ክርክር ሊነሳ ሆነ። እኔ የጻፍኩት ስለሆነ ጉድለት ኣለዉ ብዬ ኣላሰብኩም።
ስለዚህ ወድያዉ ፈገግ ብዬ ጉድለት የለዉም ያለዉን ኣረጋግቼ ጉድለት ኣላዉ ወደኣለዉ ዞሬ እሺ እስቲ ኣሻሽለዉ ኣልኩት። ለማሻሻል ሲታገል ኣየሁ። ሌሎችም ኣዩት። ኣንድ የሞከረዉ ያልተሻለ ሆነ። ሌሎች ፊት ታግሎ እንደ ነበረ ይሁን ብሎ ሁላችንም ተስማማን። ከፈገግታ ጋር።
ይህ መናገርም የማያስፈልግ ቀላል ምሳሌ ነዉ። አስተሳሰቡ የትም ስራ ላይ መዋል የሚችል ይመስለኛል።
እላ ማለት እይ ወይም ተመልከት ማለት ነዉ፣ በኣድናቆት ጭምር።
እላሜ ማለት እስቲ ስማ ወይም እስቲ እይ እንደማለት ነዉ። ከግሰጻ ጋር። ይታረም እንደማለት ነዉ።
ከዚህ የበለጠ ወይም የጠለቀ ማብራርያ ይኖረዉ ይሆናል። እኔ የገባኝን ያህል ነዉ የሞከርኩኝ። የምሞክረዉ።
በእንግልዘኛ እላ Look! ማለት ይሆናል። እላሜ Look here እንደማለት ይሆናል።
ለዚህ ጥልቅ አስተሳሰብ ግልጽ ምሳሌ ይሆናል ብዬ የማስብ የሽግግር ግዜ ኦቦ ሌንጮ ለታ ሲናገር በዜና የሰማሁኝ ነዉ።
ቃል በቃል ባይሆንም ኣንድ ቀን የሰማሁትን ንግግሩን በደንብ ኣስታዉሳለሁ።
መማር እንፈልጋለን። ከዚህ የተማርነዉ ምንም የለም ነበር ያለዉ።
የተናገረዉ ከማስታዉሰዉ ከተለየ ስህተቱ የእኔ ማስታወስ ይሆናል።
መማር እንፈልጋለን ማለቱ በኣድናቆት እላ ያምያስብል ነዉ። ያስባለኝ ነዉ። መማር እንፈልጋለን የሚል ባለስልጣን የተለመደ ኣልነበረም። ኣላስታዉስም ነበር። እናስተምራችሁ ባይ ባለስልጣን ነበር የስልጣን ባህሉ።
መማር እንፈልጋለን ማለቱን ሰምተህ እላ ብለህ ኣጣጥመህ ሳታበቃ በፍጥነት ከዚህ የተማርነዉ ምንም የለም ማለቱን ስትሳማ በቅጽበት አረ እባክህ የምያስብል ነበር። ያስባለኝ ነዉ።
በእላ ፊ እላሜ መማር እንፈልጋለን ያልከዉ እላ ያስብላል። ከዚህ የተማርነዉ ምንም የለም ያልከዉ እላሜ ያስብላል። ለምሳሌ ከዚህ ምንም የተማርነዉ ዬለም ከማለት ከእኛም እንድትማሩ እንመክራለን ብትል ኖሮ ይሻል ነበር ማለት ነዉ።
ሀሳብ የሰዉን ኣዕምሮን በቀላሉ ይረታል። በቀላሉም ግትር ያደርገዋል።
ሁሉም ሰዉ በተለያየ ደረጃ ኢጎ የምትባል ነገር ኣለዉ። በኣማርኛ ወይም አፋን ኦሮሞ ትርጉሙን ኣላዉቅም። ምናልባት ከማን ኣንሼ ይገልጸዉ ይሆናል።
እላ ስለ ግል ሳይሆን ስለ ሌላ ነዉ። ከማን ኣንሼ ስለ ሌላ ሳይሆን ስለ ግል ነዉ። ይህቺን ልዩነት ብቻ ማስተዋል መግባባትን የምያበዛ ይመስለኛል።
ጥልቅ ባህል ያለዉ ሕዝባችን እላ ፊ እላሜ ይላል። ስለ ግል ሳይሆን ስለ ሌላ ያወሳል። እኛ ትምህርት ቤት ደርሰን ከማን ኣንሼ እንላለን። ስለ ሌላ ሳይሆን ስለ ግል እናወሳለን። ሁሌ ባይሆንም ብዙ ግዜ። ለክርክር የሚበቃ ግዜ። ለክርክር የበቃ ለክርክር መቀጠል ይበቃል።
በተለይ ብዙ ሳይለፉበት ኣዲስ ሀሳብ ሲሰሙ ሳይገባቸዉ ግትር የሚሆኑ ይበዛሉ። በጥበብ እንዲገባቸዉ ማድረግ ይቻላል።
የኣጋጠመኝ ምሳሌ ኣለ። በለዉጥ ግዜ የነበረ ዕድር እንድመራ ተመርጬ የመተዳደርያ ደንብ ኣዘጋጀሁለት። አባላቱ ሀሳብ በመስጠት ማሻሻል ይችሉ ነበር። ጥቂቶች ሀሳብ በመጨመር እንዲሻሻል ኣድርገዋል።
ለማጽደቅ ተሰበሰብን። ኣንድ አባል ኣንድ አንቀጽ ጉድለት ኣለዉ የሚል ሀሳብ ኣቀረበ።
ወድያዉ ኣንብቦ እና የራሱን ሀሳቦች ጨምሮበት የነበረ አባል ጉድለት የለዉም ኣለ። ስብሰባዉን እየመራሁ ጉድለት ኣለዉ እና ዬለዉም የሚል ክርክር ሊነሳ ሆነ። እኔ የጻፍኩት ስለሆነ ጉድለት ኣለዉ ብዬ ኣላሰብኩም።
ስለዚህ ወድያዉ ፈገግ ብዬ ጉድለት የለዉም ያለዉን ኣረጋግቼ ጉድለት ኣላዉ ወደኣለዉ ዞሬ እሺ እስቲ ኣሻሽለዉ ኣልኩት። ለማሻሻል ሲታገል ኣየሁ። ሌሎችም ኣዩት። ኣንድ የሞከረዉ ያልተሻለ ሆነ። ሌሎች ፊት ታግሎ እንደ ነበረ ይሁን ብሎ ሁላችንም ተስማማን። ከፈገግታ ጋር።
ይህ መናገርም የማያስፈልግ ቀላል ምሳሌ ነዉ። አስተሳሰቡ የትም ስራ ላይ መዋል የሚችል ይመስለኛል።