Admission by Julla about the intense use of drones to bombm Amhara has put the Abiy regme in hot waters.
Posted: 15 Dec 2023, 13:35
የኢትዮጵያውያን አሜሪካውያን ሲቪክ ካውንስል ከኮንግረስማን ጆን ጀምስ ጋር በዋሽንግተን ውይይት አደረገ።
የአፍሪካ ጉዳዮች ዴሬክተር ከሆኑት እና ባለፉት ሳምንታት በኢትዮጵያ ጉዳይ የአፍሪቃን ቀንድ ልዩ መልእክተኛ የሆኑትን አምባሳደር ማይክ ሃመርን ካናገሩት ከተከበሩ ጆን ጀምስ ጋር ጥልቅ ውይይት አድርገዋል።
የምክር ቤቱ ሃላፊ ወኪሎች በወቅቱ የአምባሳደሩን እና ሌሎች ሃላፊዎችን ሪፖርትና የእለቱን ውይይት እንደገና በጥልቀት መምርመራቸውን ለካውንስሉ ወኪሎች አስረድተዋል።
ዲያቆን ዮሴፍ ተፈሪ የሪፐብሊካኑን ኮንግረስማን ጆን ጀምስን በአሁኑ ሰኣት የአለም ፖለቲካ በተለወጠበት ሰኣት እንደረሰዎት ያለ የኢትዮጵያ ወዳጅ ማግኘታችን እና ጉዳዩን ለዲሞክራሲና ለሰበኣዊ መብት መቆርቆር በቁርጠኝነት ስለያዙልን እናመሰግናለን። ኮንግረስ ቢሮው ለኛ ጀሮ ሰጥቶ በኢትዮጵያ የሚደረገውን ግፍና በደል ለማዳመጥ እና ከዛም አልፎ በቀጣይ ውይይት እንዲኖር ለምታመቻቹልን ስራ ሁሉ ምስጋናችን ከፍ ያለ ነው። የብልፅግና መንግስት ከሁለት ቀን በፊት በኢታማጆር ብርሃኑ ጁላ አማካኝነት በማንነት ላይ ያተኩረ ግድያ በአማራው ክልል ላይ ለማድረግ የሚከለክለን የለም ድሮን የገዛነው ልንገድልበት እንጂ ለጌጥ አይደለም በሚል ዛቻና ማስፈራሪያ እንዲሁም መግደላቸውን አምነዋል ስለዚህ ይህ በአስቸኳይ እንዲታይ እና የአሜሪካ መንግስት በዜጎች ላይ የሰብአዊ መብት ጥሰት በግልጽ የሚፈፅሙትን ተጠያቂ እንዲያደርግ እንጠይቃለን ብለዋል።
የኮንግረስ ሃላፊዎች እጅግ በሆነው ሁሉ ማዘናቸውን እና አሁን የተባሉትን ማስረጃዎች በአቸኳይ ካውንስሉ ለቢሮው እንዲያስገባ ወኪል ሃላፊው ተናግረዋል።
በቅርቡ በዚህ ዙሪያ ከከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ዝግ ውይይት እንደሚደረግ ቃል ገብተዋል።
የካውንስሉ የዋሽንግተን ዲሲ አመራሮች የሪፐብሊካኑን ኮንግረስማን ጆን ጀምስን በዚህ ወቅት ከጎናችን በመሆናቸው ምስጋና በመላው ኢትዮጵያን አሜሪካን መራጮች ስም ይድረሰዎት ብለዋል ስብሰባው ሲጠናቀቅ።
https://mereja.com/amharic/v2/893644
የአፍሪካ ጉዳዮች ዴሬክተር ከሆኑት እና ባለፉት ሳምንታት በኢትዮጵያ ጉዳይ የአፍሪቃን ቀንድ ልዩ መልእክተኛ የሆኑትን አምባሳደር ማይክ ሃመርን ካናገሩት ከተከበሩ ጆን ጀምስ ጋር ጥልቅ ውይይት አድርገዋል።
የምክር ቤቱ ሃላፊ ወኪሎች በወቅቱ የአምባሳደሩን እና ሌሎች ሃላፊዎችን ሪፖርትና የእለቱን ውይይት እንደገና በጥልቀት መምርመራቸውን ለካውንስሉ ወኪሎች አስረድተዋል።
ዲያቆን ዮሴፍ ተፈሪ የሪፐብሊካኑን ኮንግረስማን ጆን ጀምስን በአሁኑ ሰኣት የአለም ፖለቲካ በተለወጠበት ሰኣት እንደረሰዎት ያለ የኢትዮጵያ ወዳጅ ማግኘታችን እና ጉዳዩን ለዲሞክራሲና ለሰበኣዊ መብት መቆርቆር በቁርጠኝነት ስለያዙልን እናመሰግናለን። ኮንግረስ ቢሮው ለኛ ጀሮ ሰጥቶ በኢትዮጵያ የሚደረገውን ግፍና በደል ለማዳመጥ እና ከዛም አልፎ በቀጣይ ውይይት እንዲኖር ለምታመቻቹልን ስራ ሁሉ ምስጋናችን ከፍ ያለ ነው። የብልፅግና መንግስት ከሁለት ቀን በፊት በኢታማጆር ብርሃኑ ጁላ አማካኝነት በማንነት ላይ ያተኩረ ግድያ በአማራው ክልል ላይ ለማድረግ የሚከለክለን የለም ድሮን የገዛነው ልንገድልበት እንጂ ለጌጥ አይደለም በሚል ዛቻና ማስፈራሪያ እንዲሁም መግደላቸውን አምነዋል ስለዚህ ይህ በአስቸኳይ እንዲታይ እና የአሜሪካ መንግስት በዜጎች ላይ የሰብአዊ መብት ጥሰት በግልጽ የሚፈፅሙትን ተጠያቂ እንዲያደርግ እንጠይቃለን ብለዋል።
የኮንግረስ ሃላፊዎች እጅግ በሆነው ሁሉ ማዘናቸውን እና አሁን የተባሉትን ማስረጃዎች በአቸኳይ ካውንስሉ ለቢሮው እንዲያስገባ ወኪል ሃላፊው ተናግረዋል።
በቅርቡ በዚህ ዙሪያ ከከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ዝግ ውይይት እንደሚደረግ ቃል ገብተዋል።
የካውንስሉ የዋሽንግተን ዲሲ አመራሮች የሪፐብሊካኑን ኮንግረስማን ጆን ጀምስን በዚህ ወቅት ከጎናችን በመሆናቸው ምስጋና በመላው ኢትዮጵያን አሜሪካን መራጮች ስም ይድረሰዎት ብለዋል ስብሰባው ሲጠናቀቅ።
https://mereja.com/amharic/v2/893644