AMazing ! አሜሪካ ከሩዋንዳ ትምህርት መውሰድ አለባት ተባለ
Posted: 03 Nov 2023, 09:03
ይሄንን ውሳኔ አሜሪካም መከተል አለባት
ሩዋንዳ ለሁሉም አፍሪካውያን ከቪዛ ነፃ የጉዞ ፈቃድ ይፋ አደረገች
እንደ አውሮፓ የሼንገን ዞን የሰዎችን በነፃነት መንቀሳቀስ እና መገበያየት ለማሳደግ አህጉሪቱ የያዘችውን ዓላማ ተከትሎ ሩዋንዳ አፍሪካውያን ያለ ቪዛ ወደ ሀገሯ እንዲገቡ መፍቀዷን በትናንትናው ዕለት አስታውቃለች።
ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ ከቪዛ ነፃ የጉዞ ፈቃዱን ይፋ ባደረጉበት ወቅት፤ እምቅ አቅም ያላትና የቱሪዝም መዳረሻ የሆነችው አፍሪካ 60 በመቶው ከአፍሪካ ውጭ ባሉ ጎብኚዎች ጥገኛ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መረጃ እንደሚያሳይ ጠቅሰዋል፡፡
ካጋሜ በ23ኛው የዓለም የጉዞ እና ቱሪዝም ምክር ቤት ዓለም አቀፍ ጉባኤ ላይ ማንኛውም አፍሪካዊ በፈለገ ጊዜ ወደ ሩዋንዳ በአውሮፕላን መግባት እንደሚችልና ምንም አይነት ክፍያ እንደማይከፍልም ገልፀዋል።
"የራሳችንን አህጉራዊ ገበያ መዘንጋት የለብንም" ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ "በመጪዎቹ አስርት ዓመታት መካከለኛ አቅማችን በፍጥነት ማደጉን ከቀጠለ አፍሪካውያን የዓለም አቀፉ ቱሪዝም የወደፊት እጣ ፈንታ ይሆናሉ" ብለዋል፡፡
በዚህም ሩዋንዳ ለአፍሪካውያን የጉዞ ገደቦችን በማንሳት አራተኛዋ አፍሪካዊት ሀገር ትሆናለች ማለታቸውን ኢንዲፔንደንት ዘግቧል።
ጋምቢያ፣ ቤኒን እና ሲሼልስ ሌሎቹ ከቪዛ ነፃ የጉዞ ፈቃድ የሚሰጡ ሀገራት ናቸው።
Source: Facebook

ሩዋንዳ ለሁሉም አፍሪካውያን ከቪዛ ነፃ የጉዞ ፈቃድ ይፋ አደረገች
እንደ አውሮፓ የሼንገን ዞን የሰዎችን በነፃነት መንቀሳቀስ እና መገበያየት ለማሳደግ አህጉሪቱ የያዘችውን ዓላማ ተከትሎ ሩዋንዳ አፍሪካውያን ያለ ቪዛ ወደ ሀገሯ እንዲገቡ መፍቀዷን በትናንትናው ዕለት አስታውቃለች።
ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ ከቪዛ ነፃ የጉዞ ፈቃዱን ይፋ ባደረጉበት ወቅት፤ እምቅ አቅም ያላትና የቱሪዝም መዳረሻ የሆነችው አፍሪካ 60 በመቶው ከአፍሪካ ውጭ ባሉ ጎብኚዎች ጥገኛ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መረጃ እንደሚያሳይ ጠቅሰዋል፡፡
ካጋሜ በ23ኛው የዓለም የጉዞ እና ቱሪዝም ምክር ቤት ዓለም አቀፍ ጉባኤ ላይ ማንኛውም አፍሪካዊ በፈለገ ጊዜ ወደ ሩዋንዳ በአውሮፕላን መግባት እንደሚችልና ምንም አይነት ክፍያ እንደማይከፍልም ገልፀዋል።
"የራሳችንን አህጉራዊ ገበያ መዘንጋት የለብንም" ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ "በመጪዎቹ አስርት ዓመታት መካከለኛ አቅማችን በፍጥነት ማደጉን ከቀጠለ አፍሪካውያን የዓለም አቀፉ ቱሪዝም የወደፊት እጣ ፈንታ ይሆናሉ" ብለዋል፡፡
በዚህም ሩዋንዳ ለአፍሪካውያን የጉዞ ገደቦችን በማንሳት አራተኛዋ አፍሪካዊት ሀገር ትሆናለች ማለታቸውን ኢንዲፔንደንት ዘግቧል።
ጋምቢያ፣ ቤኒን እና ሲሼልስ ሌሎቹ ከቪዛ ነፃ የጉዞ ፈቃድ የሚሰጡ ሀገራት ናቸው።
Source: Facebook
